A I For health Sector

A I For health Sector Digital health for all Ethiopian

16ኛው የዓለም የቫይራል ሄፓታይተስ ቀን “የቫይራል ሄፓታይተስ ምርመራና ህክምና አገልግሎት ተደራሽነት ተግዳሮቶችን እናስወግድ" በሚል መሪ ቃል በጋዜጣዊ መግለጫ እና በግንዛቤ ማስጨበጫ ተከብ...
28/07/2026

16ኛው የዓለም የቫይራል ሄፓታይተስ ቀን “የቫይራል ሄፓታይተስ ምርመራና ህክምና አገልግሎት ተደራሽነት ተግዳሮቶችን እናስወግድ" በሚል መሪ ቃል በጋዜጣዊ መግለጫ እና በግንዛቤ ማስጨበጫ ተከብሯል።
_______

ቫይራል ሄፓታይተስ ቢ እና ሲ መከላከልና መታከም ስለሚችሉ ማንም ሰው በእነዚህ በሽታዎች መሞት እንደሌለበት በመድረኩ ተገልጿል።

በጤና ሚኒስቴር የኤች አይ ቪ መከላከልና መቆጣጠር መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ፍቃዱ ያደታ እንደገለጹት፣ በኢትዮጵያ የቫይራል ሄፓታይተስ ስርጭት እየጨመረ መሆኑን በተደረገ ጥናት መረጋገጡ የበሽታው ጫና እንደሚያመለክት ገልጸዋል።

ጤና ሚኒስቴር በሽታውን ለመቆጣጠር
የግንዛቤ ማስጨበጫ፣ የክትባት አቅርቦት፣ የምርመራና የህክምና ተቋማት የማስፋፋት፣ የመድሀኒትና ግብአት አቅርቦትን እንዲሁም የበለሞያ አቅምን በማጠናከር ረገድ ተከታታይ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አቶ ፍቃዱ ተናግረዋል።

የዓለም ጤና ድርጅት ተወካይ ዶ/ር ሰብለ አባተ፣ ኢትዮጵያ በ2030 ቫይራል ሄፓታይተስን ከህዝብ ጤና ስጋትነት ለማስወገድ እያደረገች ያለውን ጥረት በማድነቅ፣ ህመሙን የመከላከል፣ የምርመራና ህክምና ከጤና ሚኒስቴርና አጋሮች ጋር በመሆን ለመስራት የአለም ጤና ድርጅት እገዛውን እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።

የቅዱስ ጴጥሮስ እፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ ዶክተር አብርሃም እሸቱ በበኩላቸው፣ ሆስፒታሉ በቫይራል ሄፓታይተስና በኤች አይ ቪ ምርመራና ህክምና ትልቅ ማዕከል ያለው መሆኑን ገልጸው፣ የዘንድሮው የዓለም የቫይራል ሄፓታይተስ ቀን በሆስፒታሉ እንዲከበር መመቻቸቱ አበረታች መሆኑን ጠቅሰው አመስግነዋል።

የኢትዮጵያ የጋስትሮኤንተሮሎጂ ማህበር ፕሬዝዳንት ዶክተር ጂኪሳ ዴቤሳ ማህበሩ የመመሪያዎችን ዝግጅትት፣ ጥናትና ምርምር ማካሄድ፣ የባለሙያዎችን አቅም ግንባታ ስልጠናና የህብረተሰብ ግንዛቤን በማሳደግ ቫይራል ሄፓታይተስን ለመቆጣጠር እገዛውን እያበረከተ መሆኑን ገልጸዋል።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6V

የቻይና-አፍሪካ ሆስፒታሎች ህብረት  የትብብር ፕሮግራም በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለውን አጋርነት የበለጠ  ያጠናክራል-የኤፌድሪ ፕሬዝዳንት ክቡር ታዬ አፅቀስላሴ_________የቻይና-አ...
27/07/2026

የቻይና-አፍሪካ ሆስፒታሎች ህብረት የትብብር ፕሮግራም በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለውን አጋርነት የበለጠ ያጠናክራል-የኤፌድሪ ፕሬዝዳንት ክቡር ታዬ አፅቀስላሴ
_________

የቻይና-አፍሪካ ሆስፒታሎች ህብረት የኢንዶስኮፒክ እና የሚኒማል ኢንቬሲቭ ቀዶ-ህክምና (Minimally Invasive Surgery) የትብብር ፕሮግራም ማስጀመሪያ ስነ-ስርዓት እና የቻይና-አፍሪካ የሮቦቲክ ቀዶ-ህክምና ስልጠና ማዕከል እና የቻይና-አፍሪካ የኢንዶስኮፒክ ቴክኖሎጂ ስልጠና ማዕከል የምርቃት ስነ-ስርዓት ተካሄዷል።

የኤፌድሪ ፕሬዝዳንት ክቡር ታዬ አፅቀስላሴ በመድረኩ የመክፈቻ ንግግራቸው የቻይና-አፍሪካ ሆስፒታሎች ህብረት የትብብር ፕሮግራም በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለውን አጋርነት የበለጠ እንደሚያጠናክር ገልጸዋል።

በህክምና ዘርፍ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን ማስተዋወቅ የመንግስት ሀላፊነት መሆኑን በመግለፅ ቴክኖሎጂ በጤና ውጤቶች ላይ ያለውን ተጽዕኖ አስረድተዋል።

የጤና ሚኒስቴር የኢትዮጵያን የጤና ሪፎርም አጀንዳ ወደፊት ለማስቀጠል በቁርጠኝነት እየሰራ እንደሚገኝ የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በመድረኩ ያስረዱ ሲሆን፣ የጤና የሰው ኃይል ልማት ቅድሚያ ከሚሰጣቸው ጉዳዮች አንዱ መሆኑን ተናግረዋል።

የማሰልጠኛ ማዕከላቱ ለቀጣዩ ትውልድ የኢትዮጵያ የቀዶ ህክምና ባለሙያች ማፍሪያ ሆነው ያገለግላሉ ያሉት ዶ/ር መቅደስ፣ እነዚህ ማዕከላት ለመላው የአፍሪካ አህጉር የእውቀት እና የላቀ አገልግሎት ማዕከል (Hubs of Excellence) እንደሚሆኑም ገልጸዋል።

ዶ/ር መቅደስ በመድረኩ የቻይና ለሲንትራል ሳውዝ ዩኒቨርሲቲ ሺያንግያ ሆስፒታል፣ ለአዲስ አበባ ሲልክ ሮድ ጠቅላላ ሆስፒታል፣ ለሸንዘን ማይንድሬይ ባዮ ሜዲካል ኤሌክክትሮኒክስ ኩባንያ ምስጋና አቅርበዋል።

በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ በቻይና እና በአፍሪካ መካከል ያለው ትብብር በሁሉም ዘርፎች እያደገ መሆኑን ተናግረዋል። ቻይና እና ኢትዮጵያ በጤናው ዘርፍ ጠንካራ ትብብር መገንባታቸውን የገለጹት አምባሳደሩ፣ በጤናው ዘርፍ በሰው ኃይል ልማት ላይ አብረን መስራታችንን እንቀጥላለን ብለዋል።

የረቀቀ የቀዶ ህክምና ማሰልጠኛ ተቋሞቹ የሃገራችንን ጨምሮ ከሱዳን፣ ዩጋንዳ፣ ሊቢያ፣ እና ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የተወጣጡ ከ 30 በላይ ተሳታፊዎች በመጀመሪያ ዙር ስልጠና መስጠት ጀምረዋል።

በመድረኩ ለስልጠና አገልግሎት ላይ የሚውሉ የህክምና መሳሪያዎች ጉብኝት የተካሄደ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ እና በቻይና መካከል ያለውን ተቋማዊ ትብብር የሚያጠናክር የመግባቢያ ስምምነት ተፈርሟል።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6V

23/07/2026

"መመርመር፣ መከታተል፣ መበልፀግ፣ ራስን መንከባከብ ጤናዎን በእጆዎ ያደርጋል!" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የራስን ጤና በራስ የመጠበቅ ወር የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ
___________

"መመርመር፣ መከታተል፣ መበልፀግ፣ ራስን መንከባከብ ጤናዎን በእጆዎ ያደርጋል!" በሚል መሪ መልዕክት የራስን ጤና በራስ የመጠበቅ ወር በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ15ኛ በኢትዮጵያ ለ2ኛ ጊዜ ተከብሯል።

በአሁኑ ወቅት በሀገራችን በስፋት በማህበረሰቡ ውስጥ እየተስተዋሉ የሚገኙ ተላላፊ እና ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎችን አስቀድሞ ለመለየት፣ ለመከላከልና በወቅቱ ተገቢውን ህክምና ለመስጠት፣ የስነ ተዋልዶ፣ የእናቶች፣ የጨቅላ ህፃናትና ህፃናት እንዲሁም የአፍላ ወጣቶች ጤና እና ስነምግብ ላይ ያለውን የማህበረሰብ ግንዛቤ በማሳደግ ዜጎች የራሳቸውን ጤና በራሳቸው እንዲጠብቁ የንቅናቄ መድረኩ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው በጤና ሚኒስቴር የእናቶች ጤና ዴስክ አስተባባሪ የሆኑት ሲስተር ዘምዘም መሐመድ ገልፀዋል።

ዜጎች ቢያንስ በዓመት ሁለት ጊዜ የጤናቸውን ሁኔታ በመደበኛነት ለማወቅ በጤና ተቋም ተገኝተው አጠቃላይ የጤና ምርመራ ማድረጋቸው አስፈላጊ መሆኑን አክለው ተናግረዋል።

በፕሮግራሙ የፓናል ውይይት እና የአኖሌ እና ቦኩሸነን ጤና አጠባበቅ ጣቢያ የመስክ ጉብኝት ተደርጓል።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6V

የአማኑኤል የአእምሮ  ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል "በጎነት ለጤና፣ ፈውስ ለሁሉም" በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብሩን በይፋ አስጀምሯል ________መርሃ ግብሩን ያ...
23/07/2026

የአማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል "በጎነት ለጤና፣ ፈውስ ለሁሉም" በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም የክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብሩን በይፋ አስጀምሯል
________

መርሃ ግብሩን ያስጀመሩት የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስፈጻሚና የሆስፒታሉ ቦርድ አባል አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ፣ መንግሥት በርካታ የበጎ ፈቃድ ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ አስታውሰው ክፍለ ከተማው ከሆስፒታሉ ጋር በመቀናጀት ህብረተሰቡን ለማገልገል መዘጋጀቱን ገልጸዋል።

የአእምሮ ጤና እክል ያለባቸውን ሰዎች ማከም ከፍተኛ የበጎነትና ተግባር ነው ያሉት አቶ ታረቀኝ ወርቅነህ ሆስፒታሉ በክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት መርሃ ግብሩ ነጻ የጤና ምርመራ ማቅረቡ የሚያኮራ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።

ክፍለ ከተማው ከጤና ሚኒስቴርና ከሌሎች ተቋማት ጋር በመቀናጀት የበለጠ የተጠናከረ ሥራ መስራቱን እንደሚቀጠልም አስታውቀዋል።

የአማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ዋና ዳይሬክተር አቶ እዳኦ ፈጆ የበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለአገርና ለወገን ያለንን ሀላፊነት በተግባር የምናሳይበት የላቀ የዜግነት መገለጫ ነው ያሉ ሲሆን ሆስፒታሉ በዘንድሮው የክረምት የበጎ ፍቃድ መርሀ ግብር 67 ሺህ ሰዎችን ነጻ የጤና ምርመራና ህክምና አገልግሎት ተጠቃሚ እንደሚያደርግ አስታውቀዋል።

በዚህም ባለሞያዎች በሙያዊ ስነምግባርና በባለቤትነት ስሜት ይህን አገራዊ ሀላፊነት እንዲሚወጡ ያላቸዉን እምነት ገልጸዋል።

Website: moh.gov.et
Facebook: Ministry of Health,Ethiopia
Twitter: x.com/fmohealth
YouTube: youtube.com/
Tiktok: tiktok.com/
Telegram: t.me/M0H_EThiopia
Linkedin: lnkd.in/ewFJ6V

22/07/2026
Health is wealth
17/07/2026

Health is wealth

Ethiopia's Digital Health FutureEthiopia continues to advance its digital health transformation through innovation, AI, ...
17/07/2026

Ethiopia's Digital Health Future

Ethiopia continues to advance its digital health transformation through innovation, AI, and modern healthcare technologies. I hope to see comprehensive digital health services implemented nationwide in support of better healthcare access, efficiency, and quality.

May God bless Ethiopia and everyone working to build a healthier, digitally empowered nation. As one of the young Ethiopians who deeply supports Prime Minister Dr. Abiy Ahmed's vision, I proudly regard him as a father figure and an inspiration to our generation. I pray that God grants him wisdom and strength to continue serving Ethiopia and Africa.

Together, we can make Ethiopia a leader in Digital Health across Africa.

🇪🇹






Ethiopia's Digital Health FutureEthiopia continues to advance its digital health transformation through innovation, AI, ...
17/07/2026

Ethiopia's Digital Health Future

Ethiopia continues to advance its digital health transformation through innovation, AI, and modern healthcare technologies. As our nation accelerates digital transformation, I hope to see comprehensive digital health services implemented nationwide to support better healthcare access, efficiency, and quality. This vision aligns with Ethiopia's commitment to innovation and a stronger healthcare system for all.

May God bless Ethiopia and everyone working to build a healthier, digitally empowered nation. Together, we can make Ethiopia a leader in Digital Health across Africa.

🇪🇹

🇪🇹












17/07/2026
17/07/2026

Everything is inside health

Address

Addis Ababa
Ababa
3000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when A I For health Sector posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share