15/02/2021
የኮሮና ክትባት ተስፋዎች፣ ስጋትና ፖለቲካ
==================
ምዕራባውያን 5 ሃያል የሆኑ የኮሮና መከላከያ ክትባቶችን ሰርተናል አሉ፡፡ የመከላከል አቅማቸውም ቫይዘር 95 %፣ ሞደርና 94.8 % እና አሰትራ ዜኒካ 70.4 % ወዘተ ነው አሉን፡፡
የአሰትራ ዜኒካን ክትባት በደቡብ አፍሪካ ለተነሳው አዲሱ ዝርያ መከላከያነቱ/ፈዋሽነቱ 10-25 % ብቻ ነው ተባለ፡፡ የጆንሰን ጆንሰንም፣ የኖቫቫክስም በአድሱ የደቡብ አፍሪካ ኮሮናቫይረስ ዝርያ(B.1.351 ወይም 501.V2),) ውጤታማነታችው አነስተኛ ናቸው፡፡ የጆንሰን ጆንሰን ክትባት ቀላል የህመም ምልክቶችን ለማስቀረት አቅሙ 57 % ሲሆን፤ ናቫቫክስ ደግሞ 49 % ነው፡፡
የአሰትራ ዜኒካን ክትባት ምርምርና ስርጭት የምትመራው ጊልበርት፣ እየቀባጠረች ነው፡፡አስትራ ዜኒካ በእንግሊዝ የተነሳውን አዲሱን ቫይረስ (B.1.1.7) ጨምሮ በጥሩ ብቃት እንደሚከላከል ቢገልፁም መረጃው ላይ በርካታ ብዝታዎች አሉ፡፡ የዚህ ክትባት በአዲሱ የእንግሊዝ ዝርያ ላይ ያሳየው ውጤታማነት 21.9% ብቻ ነው፡፡
የካቲት 21/2021 የአለም የጤና ድርጅት ባወጣው መረጃ መሰረት ሀገራት በትብብር ለመስራት እያሳዩት ያለው ዳተኝነትና የራሴን ዜጋ ብቻ የሚለው የበቀል አካሄዲ ወረርሽኙ ያሉትን ክትባቶች እንዲላመዳቸው ያደርጋል እንጅ መፍትሔ አይደለም እያሉ ነው፡፡ የራስህን ዜጋ ከትበህ ሌላውን መተው ከሞራል አንፃርም ትክክል አይደለም፡፡
በአንድ ጥናት መረጃ መሰረት ክትባት ያላቸው ሀገሮች የራሳቸውን ዜጋ ቢከትቡና ክትባት የሌላቸው ሀገራት ቤታቸውን በመዝጋት ከቤታቸው ቢቀመጡ፣ ሀብታም ሀገሮች እስከ 4.5 ትሪሊዮን ዶላር እንደሚከስሩ ያመለክታል፡፡
አሁን በክትባት እየታየ ያለው የእኔ ዜጎች ብቻ ይከተቡ፤ ኢትዮጵያ ውስጥ ካለው አርቲፊሻል የእቃ አቅርቦት እጥረትና ዋጋ መናር ጋር ይመሳሰላል፡፡ ሀብታም ሀገራት ከራስ ፍላጎት በላይ ላለማምረት እያሳዩት ያለው ዳተኝነት፣ ተጨማሪ አዳዲስ ዝርያዎች እንዲፈጠሩ ከማድረግ ያለፈ ፋይዳና ትርፍ የለውም፡፡
እስከሁን ድረስ ከ30000 በላይ የጤና ባለሙያዎች በኮቪድ-19 ምክንያት ሞተዋል፡፡ አሁን ደግሞ ዘንዶው ኢቦላ ቫይረስ እንደተነሳ መረጃዎች እየወጡ ነው፡፡ የአደገኛ ጀርሞች ጭፈራና ፉከራና የአለም ዲንቀርና አስፈሪ ነው፡፡