09/05/2026
የሁለተኛ ዙር ስትራቴጂካዊ ውጤታማ የጤና አመራር ስልጠና (Strategic High Impact Leadership for Health) ተጠናቀቀ።
********************************************
የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ጋር በመተባበር ለተቋሙ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በስትራቴጂካዊ ውጤታማ የጤና አመራር (Strategic High Impact Leadership for Health) ዙርያ ከሚያዝያ 28 እስከ 30 በአዳማ ከተማ ሲሰጥ የነበረው የሁለተኛ ዙር ስልጠና ተጠናቀቀ።
የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብሩክ ነጋሽ በስልጠናው የመዝግያ ንግግር ባስተላለፉት መልዕክት፤ ስልጠናው ተቋሙ በቀጣይ የያዛቸዉን ዕቅዶች ለመከወን አይተከ ሚና እንዳለዉ ገልፀዉ ፤ በመጀመርያ ዙር የተለዩትን የፕሮጀክት ስራዎች ከተቋሙ ነባራዊ ሁነታ አንጻር እንድፈቱና ለዉጤት እንዳበቁ የሚለካ እና ችግር ፈቺ የሆኑ ሀሳቦችን በየፈርጁ በመለየት የተሻሉ ስራዎችን መስራት እንድችሉ አቅም የፈጠረላቸዉ ስልጠና መሆኑን ጠቅሰዉ ፤ በቀጣይ የተሻሉ አገልግሎቶችን ለማህበረሰቡ በመስጠትና የተገልጋዮችን ፍላጎት በማረጋገጥ የተሻለ ነገን መፍጠር የሁሉም ኋላፊነትና የዘወትር ተግባር እንደሚሆን አሳስበዉ ፤ ስልጠናው እንድሳካ የጤና ሚኒስቴር ላደረገው ድጋፍና ቅንጅት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
በጤና ሚኒስቴር የጤና ስርዓት ኢኖቬሽንና ማሻሻያ መሪ ስራ አስፈጻሚ የጤና ፍትሃዊነትና አመራር ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ አቶ ገሙ ቲሩ በበኩላቸው የጤና ሚኒስቴር በጤና ስርአት ውስጥ የጤናዉን ሰክተር ለማሻሻልና የአመራሩን ክህሎት ለማሳደግ ሰፋፊ ስራዎች እየተሰራ መሆኑን አንስተዉ ፤ የሁለተኛ ዙር ስልጠና ከመጀመርያ ዙር ስልጠና የተሻለ አቅም የተፈጠረበትና ጥሩ መነሳሳት የታየበት በመሆኑ አለም በፍጥነት እየሄደ ባለበት ልክ ሰልጣኞች የእዉቀት አድማሳቸዉን በየግዘዉ በማሳደግና የአመራር ሚናቸዉን በማጎልበት የተሻለ ተቋም መፍጠር ከሁሉም የሚጠበቅ መሆኑን ገልጸዋል።
አክለዉም አቶ ገሙ ቲሩ ለእያንዳንዱ ችግር ወደ ራሳችሁ ተቋም ነባራዊ ሁነታ በመዉሰድ ችግር ፈቺ የሆኑ ሀሳቦችን በመለየት ለዉጤት እንዲበቃ እና የተቀረጹት ፕሮጀክቶች በኮቺንግና በሙያ ትስስር በመታገዝ ከግብ እንድደርስ ሚኒስቴር መ/ቤቱ አስፈላጊዉን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ገልፀዉ ፤ ሰልጣኞች ያገኛቹትን እዉቀት በየደረጃዉ ላሉ መዋቅሮቾ በተዋረድ በማዉረድ የአመራሩን እና የባለሙያዎችን አቅም በማብቃት የተቋሙን ራዕይ እና ተልዕኮ ማሳከት የሚጠበቅባቸዉ መሆኑን አስገንዝበዉ፤ የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት አመራሩን ለማብቃትና የተሻለ የጤና ሰክተር ለመፍጠር ላሳየው ቁርጠኝነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ የሁለተኛ ዙር ስልጠና ከመጀመርያ ዙር ስልጠና የተሻለ አቅም የተፈጠረበትና ለተቀረጹት የፕሮጀክት ስራዎች ግብኣት የሚሆኑ አዳድስ ሃሳቦችን የቀሰሙበትና ለተግባር ስራዎች ጥሩ ተነሳሽነት የፈጠረላቸዉ መሆኑን ገልፀዉ፤ ያገኙትን እዉቀት መረት ላይ በማዉረድና ሌሎች ተተኪ ሠራተኞችን በማብቃት በጋራ በመሆን የተሻሉ አገልግሎቶችን ለማህበረሰቡ መስጠት እንዲችሉ አቅም የፈጠረላቸዉ ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል።