Ethiopian Prosthetic and Orthotic Service - EPOS

Ethiopian Prosthetic and Orthotic Service - EPOS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Prosthetic and Orthotic Service - EPOS, Orthotics & Prosthetics Service, Mikililand Center, Addis Ababa.

የሁለተኛ ዙር ስትራቴጂካዊ ውጤታማ የጤና አመራር ስልጠና (Strategic High Impact Leadership for Health)  ተጠናቀቀ።*******************************...
09/05/2026

የሁለተኛ ዙር ስትራቴጂካዊ ውጤታማ የጤና አመራር ስልጠና (Strategic High Impact Leadership for Health) ተጠናቀቀ።
********************************************

የጤና ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ጋር በመተባበር ለተቋሙ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች በስትራቴጂካዊ ውጤታማ የጤና አመራር (Strategic High Impact Leadership for Health) ዙርያ ከሚያዝያ 28 እስከ 30 በአዳማ ከተማ ሲሰጥ የነበረው የሁለተኛ ዙር ስልጠና ተጠናቀቀ።

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ም/ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ብሩክ ነጋሽ በስልጠናው የመዝግያ ንግግር ባስተላለፉት መልዕክት፤ ስልጠናው ተቋሙ በቀጣይ የያዛቸዉን ዕቅዶች ለመከወን አይተከ ሚና እንዳለዉ ገልፀዉ ፤ በመጀመርያ ዙር የተለዩትን የፕሮጀክት ስራዎች ከተቋሙ ነባራዊ ሁነታ አንጻር እንድፈቱና ለዉጤት እንዳበቁ የሚለካ እና ችግር ፈቺ የሆኑ ሀሳቦችን በየፈርጁ በመለየት የተሻሉ ስራዎችን መስራት እንድችሉ አቅም የፈጠረላቸዉ ስልጠና መሆኑን ጠቅሰዉ ፤ በቀጣይ የተሻሉ አገልግሎቶችን ለማህበረሰቡ በመስጠትና የተገልጋዮችን ፍላጎት በማረጋገጥ የተሻለ ነገን መፍጠር የሁሉም ኋላፊነትና የዘወትር ተግባር እንደሚሆን አሳስበዉ ፤ ስልጠናው እንድሳካ የጤና ሚኒስቴር ላደረገው ድጋፍና ቅንጅት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በጤና ሚኒስቴር የጤና ስርዓት ኢኖቬሽንና ማሻሻያ መሪ ስራ አስፈጻሚ የጤና ፍትሃዊነትና አመራር ማሻሻያ ዴስክ ኃላፊ አቶ ገሙ ቲሩ በበኩላቸው የጤና ሚኒስቴር በጤና ስርአት ውስጥ የጤናዉን ሰክተር ለማሻሻልና የአመራሩን ክህሎት ለማሳደግ ሰፋፊ ስራዎች እየተሰራ መሆኑን አንስተዉ ፤ የሁለተኛ ዙር ስልጠና ከመጀመርያ ዙር ስልጠና የተሻለ አቅም የተፈጠረበትና ጥሩ መነሳሳት የታየበት በመሆኑ አለም በፍጥነት እየሄደ ባለበት ልክ ሰልጣኞች የእዉቀት አድማሳቸዉን በየግዘዉ በማሳደግና የአመራር ሚናቸዉን በማጎልበት የተሻለ ተቋም መፍጠር ከሁሉም የሚጠበቅ መሆኑን ገልጸዋል።

አክለዉም አቶ ገሙ ቲሩ ለእያንዳንዱ ችግር ወደ ራሳችሁ ተቋም ነባራዊ ሁነታ በመዉሰድ ችግር ፈቺ የሆኑ ሀሳቦችን በመለየት ለዉጤት እንዲበቃ እና የተቀረጹት ፕሮጀክቶች በኮቺንግና በሙያ ትስስር በመታገዝ ከግብ እንድደርስ ሚኒስቴር መ/ቤቱ አስፈላጊዉን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ገልፀዉ ፤ ሰልጣኞች ያገኛቹትን እዉቀት በየደረጃዉ ላሉ መዋቅሮቾ በተዋረድ በማዉረድ የአመራሩን እና የባለሙያዎችን አቅም በማብቃት የተቋሙን ራዕይ እና ተልዕኮ ማሳከት የሚጠበቅባቸዉ መሆኑን አስገንዝበዉ፤ የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት አመራሩን ለማብቃትና የተሻለ የጤና ሰክተር ለመፍጠር ላሳየው ቁርጠኝነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው፤ የሁለተኛ ዙር ስልጠና ከመጀመርያ ዙር ስልጠና የተሻለ አቅም የተፈጠረበትና ለተቀረጹት የፕሮጀክት ስራዎች ግብኣት የሚሆኑ አዳድስ ሃሳቦችን የቀሰሙበትና ለተግባር ስራዎች ጥሩ ተነሳሽነት የፈጠረላቸዉ መሆኑን ገልፀዉ፤ ያገኙትን እዉቀት መረት ላይ በማዉረድና ሌሎች ተተኪ ሠራተኞችን በማብቃት በጋራ በመሆን የተሻሉ አገልግሎቶችን ለማህበረሰቡ መስጠት እንዲችሉ አቅም የፈጠረላቸዉ ስልጠና መሆኑን ተናግረዋል።

30/04/2026
የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት   የመንግስት ሰራተኞች አዋጅና ተዛማጅ ህጎች ዙሪያ ለአጠቃላይ ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።*******************************...
29/04/2026

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት የመንግስት ሰራተኞች አዋጅና ተዛማጅ ህጎች ዙሪያ ለአጠቃላይ ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።
**********************************************

በኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የህግ አገልግሎት መሪ ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፊን ረጋሳ ስልጠናዉን የሰጡ ሲሆን ፤ የመንግስት ሠራተኞች አዋጅና ተዛማጅ ህጎች እና በተሻሻለው አዋጅ 1353/2017 ዓ.ም ዙሪያ የመንግስት መስሪያ ቤቶች የተሰጣቸውን ኃላፊነት፣ ተግባርና ተልዕኮ በብቃት፣ በጥራትና በውጤታማነት እንዲወጡ ከማድረግ ባለፉ ዘመናዊ የአሠራር ስርዓትን በመከተል፣ ለተገልጋዩ ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ የሚረዳ መሆኑን አስረድተዉ ፤ አዋጁ የመንግስት አገልግሎትና አስተዳደር ስራን ለማሻሻል ፣ ምርታማነትን ለመጨመርና ለማጎልበት እንዲሁም ብቃት ያላቸውን ባለሙያዎች ለማግኘትና ለማቆየት አስፈላጊ መሆኑን
አቶ መስፊን ረጋሳ ገልጸዋል።

ስልጠናዉ ፤በፊት ከነበራቸው እውቀት የተሻለ ግንዛቤ ያገኙበት እና በቀጣይ የተቋሙን ራዕይ ለማሳካት አቅም የፈጠረላቸዉ መሆኑንና በተመደቡበት የስራ ቦታ የተሻሉ ስራዎችን መስራት እንድችሉ የሚያግዝ መሆኑን የስልጠናዉ ተሳታፊዎች ገልጸዋል።

29/04/2026

በጤናው ዘርፍ የተመዘገቡ እድገቶች


28/04/2026

የጤና ሚኒስትሯ ዶ/ር መቅደስ ዳባ ባለፉት ስምንት የለውጥ ዓመታት በጤና ዘርፍ የተመዘገቡ ዓበይት ስኬቶችን ባቀረቡት ሪፖርት፦ ዘርፉ ከለውጡ በፊት የነበሩ ክፍተቶችን በመለየት ካስመዘገባቸው ዋና ዋና ስኬቶች መካከል፤ ለ30 ዓመታት የቆየው የጤና ፓሊሲን በመከለስ፣ መከላከል ከሚለው መርህ በተጨማሪ አክሞ የማዳን ቁርጠኛ የፖሊሲ አመራር፣ የተቋም ግንባታ፣ የጤና መሠረተ ልማት ለውጦች፣ መድሃኒት፣ ክትባት እና የህክምና ግብዓቶች ምርት አቅርቦት እና ቁጥጥር ጭማሪ እንዲሁም የጤና ፋይናንስ እመርታ ቁልፍ እና ዋነኞቹ የለውጥ ስራዎች ናቸው።

‎በተለይም የወረርሽኝ ልየታ እና ቁጥጥር፣ የመጀመሪያ ደረጃ የጤና እንክብካቤ፣ የጤና ባለሙያዎችን ማብቃትና ቁጥራቸውን ማሳደግ፤ የዲጂታል ጤና፣ በዘርፉ የተተገበሩ ልዩ ልዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች ኢትዮጵያ በጤና ዘርፍ ያስመዘገበቻቸው ግንባር ቀደም ስኬቶቿ ናቸው።

የጤና ዲፕሎማሲ ዘርፍ ከፍ ያሉ እመርታዎች የተመዘገበበት አንዱና ዋነኛው መስክ ሲሆን ኢትዮጵያ በተለያዩ መድረኮች ከአፍሪካ በቀዳሚነት ተመርጣ ድርድሮችን እና ንግግሮችን እንድትመራ አስችሏታል።

የአገልግሎቱ የስራ እንቅስቃሴ+++++++++++++++++++++++++++አዲስ ዘመን ጋዜጣ ፤ሰኞ ሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓም.
27/04/2026

የአገልግሎቱ የስራ እንቅስቃሴ
+++++++++++++++++++++++++++

አዲስ ዘመን ጋዜጣ ፤ሰኞ ሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓም.

23/04/2026
በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሳሀረላ አብዱላሂ የተመራ ቡድን የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎትን ጎበኙ።****   ****  ****    ****   *****  *****  *...
16/04/2026

በጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሳሀረላ አብዱላሂ የተመራ ቡድን የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎትን ጎበኙ።
**** **** **** **** ***** ***** *** *****

የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሳሀረላ አብዱላሂ በኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት እየተሰሩ ያሉ ስራዎችንና በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራትን ብሎም የመሠረተ ልማት ፕሮጀክት ስራዎችን፤ የተመዘገቡ ስኬቶችን፤ በዘርፉ የሚታዩ ተግዳሮቶችን እና በቀጣይ ሊሰሩ በታቀዱ ስራዎች ዙሪያ ከኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ታሪኩ ታደሰ እና ከተቋሙ የማናጅመንት አባላት ጋር ሰፊ ውይይት አድርገዋል።

በውይይቱ በተቋሙ እየተሰሩ ያሉትን ስራዎች ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሳሀረላ አብዱላሂ አድንቀው፤ በቀጣይ ተቋሙ ያቀደውን የሚያሳካበትን ሀገራዊና ተቋማዊ አጀንዳዎች በአጭር፣ በመካከለኛ እና በረጅም ጊዜ እቅድ በመለየት እንዲፈቱ ጤና ሚኒስቴር በልዩ ትኩረት እንደሚሰራ ገልጸዉ፤ በቀጣይም የተቋሙን ራዕይ እዉን ለማድረግ እንዲቻል ከሌሎች መንግስታዊና መንግሰታዊ ያልሆኑ አጋር ድሪጂቶች ጋር በመተባበር እንዲሰራና ተቋማዊ ፊላጎቶቹ ከግብ እንዲደርሱ ጤና ሚኒስቴር ሙሉ በሙሉ የሚደግፍና ከምን ጊዜዉም በላይ የሚሰራ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ሳሀረላ አብዱላሂ ገልጸዋል።

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።          ******መልካም በዓል!*******            ****Happy Easter!****
11/04/2026

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

******መልካም በዓል!*******
****Happy Easter!****

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችን ለመድኅኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት  በዓል በሰላም አደረሳችሁ!              *****መልካም በዓል!*****
10/04/2026

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችን ለመድኅኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
*****መልካም በዓል!*****

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር አካሄደ።****  *****  ******  ******   ***** *****የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከአዲስ ከተማ ክ...
09/04/2026

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር አካሄደ።
**** ***** ****** ****** ***** *****

የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ከአዲስ ከተማ ክ/ከ የወረዳ 13 ጋር በመተባበር የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአዲስ ከተማ ክ/ከ ለወረዳ 13 የፀጥታ አካላት እና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸዉ ለአካባቢው ማህበረሰብ ከስዲስት መቶ ሺህ ብር በላይ የሚገመት በሬ፣ ዱቄትና ዘይት ድጋፍ አደረገ።

በድጋፉ የተገኙት የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ታሪኩ ታደሠ እንደገለጹት እንደ ተቋም "ሰው ተኮር" ስራዎችን መስራት አስፈላጊ መሆኑን ተገንዝበን የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ በአዲስ ከተማ ክ/ከ ለወረዳ 13 የፀጥታ አካላት እና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸዉ ለአካባቢው ማህበረሰብ ድጋፍ ማድረጋቸዉ ተቋማዊና ማህበራዊ ግንኙነትን የሚያጎለብት መሆኑን ገልጸዉ፤ ካለባቸዉ ድሪብ የሰራ ኋላፊነት እና የኑሮ ሁነታ አንፃር በበዓል ወቅት ከቤቴሰቦቻቸዉ ጋር ደስተኞች ሆነዉ በዓሉን እንዲያሳልፉ እና እንደ ተቋም ከጎናቸዉ መሆናችንን በተግባር ለማሳየት ታስቦ የተዘጋጀ ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር መሆኑን ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶ/ር ታሪኩ ታደሠ ገልፀዉ ፤ለመላዉ የክሪስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ ለስቅለት እና ለትንሳኤ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በአዲስ ከተማ ክ/ከ የወረዳ 13 ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አለማየው ምርገሳ እንደተናገሩት የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ ለወረዳ 13 የፀጥታ አካላት እና ዝቅተኛ ገቢ ላላቸዉ ለአካባቢው ማህበረሰብ ላደረገዉ የማዕድ ማጋራት መርሃ-ግብር አመስግነዉ፤ ተቋሙ መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ተቋማዊ መስተጋብሪን የበለጠ በማጠናከር ከወረዳዉ ጋር የተለያዩ የልማት እና ሰው ተኮር ተግባራትን እያከናወነ መሆኑን ገልፀዉ ፤ በቀጣይም መሰል ሰዉ ተኮር ስራዎችን አጠናክሮ እንዲያሰቀጥሉ ጠይቋል።

ድጋፋ የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት የማኔጅመንት አባላትና የወረዳው አመራሮች በተገኙበት ተካሂዷል።

Address

Mikililand Center
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Prosthetic and Orthotic Service - EPOS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share