24/08/2026
"ደም ይለግሱ ህይወት ያድኑ" በሚል መሪ ቃል የደም ልገሳ መርሃ ግብር ተካሄደ።
*************************************
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 18፣ 2018
የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች የጤናዉን ዘርፍ የክረምት በጎ ፈቃድ ጥሪ በመቀበል “ደም ይለግሱ፤ ህይወት ያድኑ!” በሚል መሪ ቃል የደም ልገሳ መርሃ ግብር አከናወኑ።
በመርሃ ግብሩ ፈቃደኛ ከሆኑ የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት አመራሮችና ሰራተኞች አስፈላጊው የጤና ምርመራ ከተደረገ በኋላ 30 ዩኒት ደም የተሰበሰበ ሲሆን አንድ (1) ዩኒት ደም የ3 (ሶስት) ሰዎችን ህይወት መታደግ ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ የደም ልገሳ መርሃ ግብር ደም ለሚያስፈልጋቸው ወገኖች በተለይም በወሊድና በተለያዩ ምክንያት የጤና እክል ላይ ለሚገኙ ሰዎች ህይወትን ለማዳን የሚያግዝ የሰብዓዊነትና የኃላፊነት ተግባር ሲሆን በብዙ ሰዎች ህይወት ላይ የሚፈጥረዉ አስተዋጽኦ ከፊተኛ ነዉ።
የኢትዮጵያ የአካል ድጋፍ አገልግሎት በክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች የማገገሚያ ህክምና አገልግሎትን ብቻ ሳይሆን ፣ሰብዓዊነትን፣በጎ ፍቃድ ስራዎችን እና የማህበረሰብ ኃላፊነትን በተግባር በመወጣት ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
👉 እርስዎም ደምዎን ይለግሱ፤ ህይወት ያድኑ! 🩸🩸 🩸
--------------------------
Website:epos.gov.et
Facebook : Ethiopian Prosthetic and Orthotic Service (EPOS)
Youtube :
https://youtube.com/?si=bmpFx6IkCOZqHzqz
TikTok: www.tiktok.com/ 2014
Telegram:https://t.me/ethiopianprostheticorthoticservi