R.I.P

R.I.P ለቤተሰባቸው፣ ለጓደኞቻቸው እንዲሁም ለአፍቃሪዎቻቸው ትልቅ The objective of this page is perpetuate our dead believers and reminded them.

This page allow each Associates valued to post stories about their relatives and friends who passed away to stay our memories.
የዚህ ገጽ ዓላማ በህይወት የሌሉ ወገኖችን በዘላቂ ሁኔታ ለማሰብ ነው ፡፡
ይህ ገጽ እያንዳንዱ ተጓዳኝ ትዝታዎቻችንን ለማቆየትና የሟች ዘመዶቻቸው እና ጓደኞቻቸው ታሪኮችን ለማስቀመጥ እንዲሁም ታሪኮችን ለማቆየት ያስችላቸዋል።

ልብ ሰባሪ አሳዛኝ ዜና 😭እናታችን ዶክተር አበበች ጎበና አረፉ አዳዬ - ነብስ ይማር The extraordinary women of our planet, Mother Tesesa of Africa, Dr...
04/07/2021

ልብ ሰባሪ አሳዛኝ ዜና 😭
እናታችን ዶክተር አበበች ጎበና አረፉ
አዳዬ - ነብስ ይማር
The extraordinary women of our planet, Mother Tesesa of Africa, Dr Abebech Gobena passed away today this morning.
ላደረጉት መልካምነት ወደር ለሌለው ደግነት
እናመሰግናለን 🙏

አርቲስት መስፍን ጌታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ********************አርቲስት መስፍን ጌታቸው በኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በኮቪድ-19 ምክንያት በተወለደ በ50 አ...
25/04/2021

አርቲስት መስፍን ጌታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ
********************

አርቲስት መስፍን ጌታቸው በኤካ ኮተቤ ሆስፒታል በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በኮቪድ-19 ምክንያት በተወለደ በ50 አመቱ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።

አርቲስት መስፍን ጌታቸው በርካታ የጥበብ ስራዎችን በድርሰት፣ በአዘጋጅነት እና በትወና ለአገሩ ያበረከተ ሁለገብ ባለሞያ ነበር።

አርቲስቱ በኢትዮጵያ ሬድዮ ዝነኛ የነበረው የቀን ቅኝት ድራማ ደራሲ እንዲሁም በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያገኘው የሰው ለሰው ተከታታይ ድራማ ደራሲ እና ተዋናይ ነበር።

አርቲስት መስፍን ጌታቸው የዙምራ ፊልም፣ መንታ መንገድ የሬድዮ ተከታታይ ድራማ እና ሌሎችም ስራዎችን በተለያዩ የቴሌቪዥን እና የሬድዮ ጣቢያዎች ለህዝብ ማድረስ ችሏል።

አርቲስት መስፍን ጌታቸው ባለትዳር እና የሶስት ልጆች (የሁለት ሴት እና የወንድ ልጅ) አባት ነበር።

አርቲስት መስፍን ጌታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡**********************የዙምራ ፊልም፣ የሰው ለሰው እና የዘመን ድራማ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎች ደራሲና ተዋናይ የነበረው ...
25/04/2021

አርቲስት መስፍን ጌታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ፡፡
**********************
የዙምራ ፊልም፣ የሰው ለሰው እና የዘመን ድራማ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎች ደራሲና ተዋናይ የነበረው አርቲስት መስፍን ጌታቸው ህይወት ማለፉን ከወዳጁ Misganaw Tadesse ሰምተናል፡፡

ለአርቲስቱ ቤተሰቦች፣ወዳጅ እና አድናቂዎች ልባዊ መፅናናትን እንመኛለን፡፡

የቀድሞው የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ ሃላፊ የነበሩትአቶ ጸጋዬ ሃይለማሪያም ዛሬ በሞት ተለይተዋል።Via ሽዋዬ ከፍያለው
15/04/2021

የቀድሞው የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ ሃላፊ የነበሩትአቶ ጸጋዬ ሃይለማሪያም ዛሬ በሞት ተለይተዋል።
Via ሽዋዬ ከፍያለው

  | የኮሪያው እና የኮንጎው ዘማች ኮሎኔል መለሰ ተሰማ በ90 አመታቸው አረፉ  ከእዝራ እጅጉ ትውልዳቸው በሲዳሞ አለታ ወንዶ ነው፡፡ ኮሎኔል መለሰ ተሰማ፡፡  ታህሳስ 30 2013 አ.ም የ9...
11/04/2021

| የኮሪያው እና የኮንጎው ዘማች ኮሎኔል መለሰ ተሰማ በ90 አመታቸው አረፉ

ከእዝራ እጅጉ
ትውልዳቸው በሲዳሞ አለታ ወንዶ ነው፡፡ ኮሎኔል መለሰ ተሰማ፡፡ ታህሳስ 30 2013 አ.ም የ90ኛ አመት የልደት በአላቸውን አክብረው ነበር፡፡ ነገር ግን የሰው ልጅ እድሜ ፈጣሪ ጋር ነውና ሮብ መጋቢት 29 2013 ህይወታቸው አልፏል ፡፡ ኮሎኔል መለሰ ተሰማ የኮሪያ ዘማቾች ማህበር ፕሬዚዳንት በመሆኑ ያገልግሉ ነበር፡፡ ሀገራቸውን የሚወዱና ያለፈውን የማስታወስ ክህሎታቸውም በብዙዎች የሚደነቅ ነበር፡፡

ኮሎኔል መለሰ ተሰማ ፣ከዛሬ 90 አመት አስቀድሞ በታህሳስ 30 1923አ.ም በሲዳሞ አለታ ወንዶ ተወለዱ፡፡ በልጅነታቸውም አባ ዘውገ ከሚባሉ መምህር ዘንድ ቀርበው ዳንዴ ጊዮርጊስ አጠገብ የፊደል ገበታ የተቋደሱ ናቸው፡፡ በጊዜው ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ወርራ ስለነበር ወረራውን በመስጋት በአባ ገብረስላሴ መምህርነት የፊደል ቆጠራ ትምህርታቸውን በመቀጠል ዳዊት ደግመዋል፡፡

ፋሺስት ድል ከሆነም በኋላ ወደ አዲስ አበባ በመምጣት ላዛሪስት በኋላም ቅድስት ማሪያም ተብለው በሚጠሩ ተማሪ ቤቶች የ1ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ተምረዋል፡፡ በ1934 አ.ም አ.ም በተፈሪ መኮንን ተማሪ ቤት በመግባት እስከ 1941 ድረስ ዘለቁ፡፡

ለወታደራዊ መኮንንነት የሚያበቃ የጽንሰ-ሀሳብና የተግባር ትምህርት ለ3 አመታት /ከ1941-1943/ ተከታትለውም በምክትል መቶ አለቃነት ማእረግ ተመረቁ፡፡

ኮሎኔል መለሰ ተሰማ ፣የጦር ወታደራዊ ትምህርትን ካጠናቀቁ በኋላ ኮሪያና ኮንጎ ዘምተው ግዳጃቸውን የተወጡ ናቸው፡፡ በ1955 በአየር ወለድ የኮማንዶ ትምህርት ተከታትለው የምስክር ወረቀት አግኝተዋል፡፡

በኢትዮጵያ ንጉሰ-ነገስት መንግስት የጦር ሀይሎች የአዛዥነት የመምሪያ መኮንንነት ኮሌጅ የተሰጠውን ትምህርት በመከታተል በ1956 ተመርቀዋል፡፡ባገኙት ውጤትም በኮሌጁ በአሰልጣኝነት እና በአዛዥነት እንዲቆዩ ተደርጓል፡፡

በኮሪያ ዘመቻ ወቅት በግንባር ቀደምትነት የተሰለፈው የንጉሰ-ነገስቱ የክብር ዘብ ሲሆን በዚህ ጦርነት ላይ ኮሎኔል መለሰ የላቀ ሚና አበርክተዋል፡፡

ከዛሬ 65 አመት በፊት ሀገራችን ኢትዮጵያ በኮሪያ በሰላም ማስከበር ሂደቱ ላይ ስትሳተፍ በደማቅ ብእር የተጻፈውን ገድል ካከናወኑ ሀገር ወዳዶች አንዱ ናቸው፡፡ ኮሎኔል መለሰ ተሰማ ባለትዳር እና የ6 ልጆች አባት ነበሩ፡፡

‹‹ተናፋቂ ትዝታችን›› የተሰኘው የኮሎኔል መለሰ መጽሀፍ በተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽን አማካይነት በ360 ደቂቃዎች በኦድዮ ሲዲ ተዘጋጅቶ የወጣ ሲሆን ተወዳጅ ሚድያ እና ኮሚኒኬሽንንም በታሪካዊ ጉዳዮች በቅርበት በማማከር ቃለ-መጠይቆችንንም በመስጠት ቀና ትብብር ያሳዩ ሀገር ወዳድ ናቸው፡፡

ኮሎኔል መለሰ ተሰማ ረቡዕ መጋቢት 29 ቀን 2013 በ90 አመት እድሜያቸው ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን የቀብር ስነ-ስርአታቸውም ቅዳሜ ሚያዝያ 2 ቀን 2013 አ.ም በመንበረ-ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ከቀኑ በ6:00 ሰአት ይፈጸማል፡፡

አሳዛኝ ዜናየ 12 ዓመቱ ብላቴና ጆሽዋ ህይወቱ አልፏል❗️ለወላጆቹ እንዲሁም በብዙ ሃዘንና  ጸሎት ለ19 ቀናት አብራችሁ ለነበራችሁ በሩቅም በቅርብም ያላችሁ ወዳጅ ዘመዶች ሁሉ መጽናናት ይሁን...
11/04/2021

አሳዛኝ ዜና

የ 12 ዓመቱ ብላቴና ጆሽዋ ህይወቱ አልፏል❗️

ለወላጆቹ እንዲሁም በብዙ ሃዘንና ጸሎት ለ19 ቀናት አብራችሁ ለነበራችሁ በሩቅም በቅርብም ያላችሁ ወዳጅ ዘመዶች ሁሉ መጽናናት ይሁን ።

ጆሽዋ ኃይለኢየሱስ ይባላል ገና የ12 ዓመት ታዳጊ ነው:: በቲክቶክ የተሰራጨ ብላክ አውት ቻሌንጅ ጨዋታ ጏደኞቹ ሲጫወቱ ያይና እሱም ካልተጫወትኩ ይላል:: ይህ ጨዋታ ራስን ለተወሰኑ ጥቂት ደቂቃዎች ሳይተነፍሱ ለመቆየት የሚደረግ ፉክክር ነው:: ጆሽዋ ይሞክረዋል ነገር ግን መጨረሻው አላማረም!! ጆሽዋ በድርጊቱ ራሱን ሳተ ከፍተኛ የአእምሮ ጉዳት ደረሰበት::

ከ 19 ቀን የህክምና ክትትል በኋላ ህይወቱ አልፏል ❗️

ዶ/ር አይናለም አብርሃ በኮቪድ-19 ህይወታቸው አለፈ።በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስ ኮሌጅ በመምህርነት እና በካንሰር ሕክምና ዘርፍ ያገለግሉ የነበሩት ዶ/ር አይናለም አብርሃ በኮቪድ...
09/04/2021

ዶ/ር አይናለም አብርሃ በኮቪድ-19 ህይወታቸው አለፈ።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጤና ሳይንስ ኮሌጅ በመምህርነት እና በካንሰር ሕክምና ዘርፍ ያገለግሉ የነበሩት ዶ/ር አይናለም አብርሃ በኮቪድ-19 ምክንያት ህይወታቸው ማለፉን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የዶክተር አይናለም አብርሃ ሕልፈት ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ እና ለሀገሪቱ ትልቅ ጉዳት ነው ብሏል ሚኒስቴሩ ባወጣው የሃዘን መግለጫ።

ዶክተር አይናለም ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በመምህርነት እና በጥቁር አንበሳ ስፕሺያላይዝድ ሆስፒታል በካንሰር ሕክምና ከፍተኛ ባለሙያነት እንዲሁም በአአዩ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የካንሰር ሕክምና ማእከል ሐላፊ በመሆን ለበርካታ አመታት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።

የጤና ሚኒስቴር በዶ/ር አይናለም አብርሃ ሕልፈተ ሕይወት የተሰማውን ሐዘን ገልጿል።

የማንዶሊኑ ተጫዋቹ - ወይ ካሊብሶ አርፈዋል 🎼 🎻አንጋፋው ድምፃዊ፣ የዜማ እና የግጥም ደራሲ፣ እንዲሁም የማንዶሊኑ ንጉስ  አየለ ማሞ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ዛሬ መጋቢት 29 ቀን 2013 ዓ....
07/04/2021

የማንዶሊኑ ተጫዋቹ - ወይ ካሊብሶ አርፈዋል

🎼 🎻
አንጋፋው ድምፃዊ፣ የዜማ እና የግጥም ደራሲ፣ እንዲሁም የማንዶሊኑ ንጉስ አየለ ማሞ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ዛሬ መጋቢት 29 ቀን 2013 ዓ.ም. ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።

የቀብር ሥነ ሥርዓቱ ነገ መጋቢት 30 ቀን 2013 ዓ.ም. በቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ይፈፀማል ተብሏል።
... በሃገራችን ኢትዮጵያ በሙዚቃው ዘርፍ ታላቅ አስተዋፅኦ እያደረጉ ካሉት የሙዚቃ ስዎች አንዱ የግጥምና የዜማ ደራሲ ፣እንዲሁም ብቸኛው የማንዶሊን ተጫዋች አርቲስት አየለ ማሞ ናቸው።

አርቲስቱ የተወለዱት ጥር 12 ቀን 1934 ዓ.ም ሲሆን ወደ ሙዚቃው ዓለም ከመግባታቸው በፊት አዲስ አበባ ደብር አሜን ተክለሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን በድቁንና ሙያ አገልግለዋል።

ከጥር 1 ቀን 1949 ዓ.ም ጀምሮ በቀድሞ የክብር ዘበኛ ሙዚቃ ክፍል በመቀጠር የተለያዩ የብሄር ብሄረሰቦችን ዘፈን በመዝፈን ይጀምሩና በመቀጠልም በዘመናዊና ባህላዊ ተወዛዋዥነት በመስራት እስከ አስልጣኝነት ተጉዘዋል።

አርቲስቱ በነበራቸው ሁለገብ እንቅስቃሴ ድምፃዊ ደስአለኝ መላኩ (ባላገሩ) ፤ አቦነሽ አድነው ፤ ኃይልዬ ታደሰን ያፈሩ አንጋፋ ባለሙያ ናቸው።

በተለይ አርቲስቱን ልዩ በሚያደርጋቸው የማንዶሊን የሙዚቃ መሳርያ "ወይ ካሊብሶ" በሚለው ዘፈናቸው የሚታወቁ ሲሆን በመጀመሪያ የተጫወቱት ዜማ ግን "የኔውብ አይናማ "የሚል ሲሆን ወዲያው በማከታተል "ያለሰለሴ ባዬቲ" ኦሮምኛ ፣ በመቀጠልም " እማማ ድንብሎ" የሚል ጉራጊኛ መድረክ ላይ ተጫውተዋል።

በውጭ ሃገራትም ኩባ፣ ስውዲን፣ ዴንማርክ፣ ጀርመን በመሄድ ሙያውን በተግባር ያስመሰከሩ ፣ የጥበብን ፀጋ የተላበሱ ሁለገብ አርቲስት ናቸው።

አርቲስት አየለ ማሞ ክብር ዘበኛ የሙዚቃ ክፍልን ለ 34 ዓመታት ያገለገሉ ሲሆን ክፍሉ ከፈረሰ በኋላ ከ1988 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 1998 ዓ.ም ለ10 ዓመት "በክስታኒ ባንድ" በኃላፊነትና በሙያቸው አገልግለዋል።

ክስታኒ ባንድ ካፈራቻቸው ወጣት አርቲስቶችም መካከል ድምፃዊ ጎሳዬ ተስፋዬ ፣ አብነት አጎናፍር፣ ፀጋዬ ስሜ (ኦሴ ባሳ) ፣ሙዚቀኛ ደስአለኝ ታደሰ ፣ ሙዚቃ አቀናባሪው መሐመድ ኑር ሁሴን የሚጠቀሱ ናቸው።

አርቲስቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰሩት ዜማ "አሸብርቆ ደምቆ እንደፀሐይ"የሚለው ሲሆን ይህንንም ጥሩ አድርጋ የተጫወተችው ብዙነሽ በቀለ ናት።

አርቲስት አየለ ማሞ በግጥምና በዜማ ስራቸው ከሰጣቸው አንጋፋና ወጣት ድምፃውያን መካከልም ድምፃዊ ጥላሁን ገሠሠ፣ መሐሙድ አህመድ ፣ ብዙነሽ በቀለ ፣ኩኩ ሰብስቤ ፣ኤፍሬም ታምሩ ፣ሀመልማል አባተ ፣ብፅአት ስዩም ፣ ወረታው ውበት ፣ አስቴር ከበደ ፣ እያዩ ማንያዘዋል ፣ ሻምበል በላይነህ፣ ደረጀ ደገፋው ፣ጌታቸው ጋዲሳ ፣ ህብስት ጥሩነህ፣ ምንያህል ጥላሁን ገሠሠ ፣ውብሻው ስለሺ፣ መንበረ በየነ ፣ ትዕግስት ይልማ ፣ከበቡሽ ነጋሽ (ሚሚ) ፣ ገነነ ኃይሌ፣ ጌታቸው ተካ ፣ ዓለማየሁ ግዛው...የሚያስታውሳቸው የስራቸው ተቃዳሾች ሲሆኑ አሁንም ለወጣት አርቲስቶች የግጥምና የዜማ ሥራቸውን ሰጥተዋል።

አርቲስቱ በአሁኑ ሰዓት ከግጥምና ዜማ ስራቸው ጎን ለጎን "አዲስ አኩስቲክ ፕሮጀክት"በማንዶሊን ተጫዋችነት አገልግለዋል።

አርቲስት አየለ ማሞ ከ1949 ዓ.ም ጀምሮ ለ64 ዓመት በሙዚቃ ህይወት ተጉዘዋል።

ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) አረፉ❗️የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ እና የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የበላይ ጠባ...
06/04/2021

ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) አረፉ❗️

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ እና የመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የበላይ ጠባቂ ብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ (ዶ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡

ከአባታቸው ከባራምባራስ ተስፋ ተክሉ እና ከእናታቸው ከወ/ሮ ታህሣ ኃይሉ በ1930 ዓ.ም ግንቦት ወር በትግራይ ክልል ብዘት ወረዳ የተወለዱት ብፁዕነታቸው በተወለዱ በ83 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸውን ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

የብፁዕ አባታችን በረከት ይደርብን፡፡

© EOTC TV

የታንጎ ሙዚቃ ቤት ባለቤት አሊ ታንጎ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ ***************  ለበርካታ የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች መነሻ የሆነው የታንጎ ሙዚቃ ቤት መስራችና ባለቤት ዓሊ አብደላ ኬይፋ ...
28/03/2021

የታንጎ ሙዚቃ ቤት ባለቤት አሊ ታንጎ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
***************

ለበርካታ የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች መነሻ የሆነው የታንጎ ሙዚቃ ቤት መስራችና ባለቤት ዓሊ አብደላ ኬይፋ (አሊ ታንጎ) በተወለዱ በ79 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

የኢትዮጵያ ሙዚቃና ሙዚቀኞች ባለውለታ የሆኑት ዓሊ አብደላ ኬይፋ (አሊ ታንጎ) ባደረባቸው ህመም በሀገረ አሜሪካ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ነው በትላንትናው እለት ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት።

ከየመናዊ አባታቸው እና ከኢትዮጵያዊት እናታቸው በጅማ ከተማ የተወለዱት ዓሊ አብደላ ኬይፋ ከ1973 ዓ.ም እስከ 1977 ዓ.ም ብቻ 53 የሚሆኑ የሙዚቃ ሥራዎችን አሳትመው ለሕዝብ አቅርበዋል።

ዓሊ ታንጎ የክቡር ዶ/ር ጥላሁን ገሠሠን የሙዚቃ ስራዎች ጨምሮ የአስቴር አወቀ፣ መሀሙድ አህመድ፣ ሐመልማል አባተ፣ ብዙነሽ በቀለ፣ የሂሩት በቀለ፣ ነዋይ ደበበ፣ አለማየሁ እሸቴ፣ ኃይሉ ዲሳሳ፣ ገመቹ ኢታና እነ አሊ ቢራ እና የሌሎች የበርካታ ዘፋኞችን ሸክላና ካሴት በማሳተም በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅና ታዋቂ እንዲሆኑ በማድረግ የላቀ ድርሻ አላቸው።

አሊ ታንጎ ባለትዳር እና የ12 ልጆች አባት ነበሩ።

ዓሊ አብደላ ኬይፋ በአሜሪካ ሲያትል ዋሽንግተን በሚገኝ የሙስሊም መቃብር ስፍራ የቀብር ስነ-ስርአታቸው ተፈፅሟል።

መጋቢት 18/1980በማይረሳ ታለቅ ተጋድሎ ህይወታቸውን በጀግንነት የሰጡን ኢትዮጵያዊ ጀግና ብርጋዴር ጄነራል ለገሠ እበጄ የመስዋዕትነት ቀን!!እኔ እኝህን የሀገራችንን ታላቅ ሰው ብርጋዴር ጄ...
28/03/2021

መጋቢት 18/1980
በማይረሳ ታለቅ ተጋድሎ ህይወታቸውን በጀግንነት የሰጡን ኢትዮጵያዊ ጀግና ብርጋዴር ጄነራል ለገሠ እበጄ የመስዋዕትነት ቀን!!

እኔ እኝህን የሀገራችንን ታላቅ ሰው ብርጋዴር ጄነራል ለገሠ አበጄን በቅርበት ለማወቅ ዕድል ካገኙ ሰዎች መካከል አንዱ በመሆኔ ሁሌም ኩራት ይሰማኛል::
ጄነራል ለገሠን የማውቃቸው ኤርትራ ክ/ሀገር / ሰራዬ አውራጃ /መንደፈራ በኮሎኔልነት ማዕረግ የ 503ኛ ሀ ንዑስ ግብረ ኅይል አዛዥ በነበሩበት ዘመን ነው::
ጄነራል መኮንኑ በህይወት ዘመኔ ፍፁም እንዳልረሳቸው ሆነው በአዕምሮዬ ውስጥ ከገዘፉ ምርጦቼ ኢትዮጵያውያን መካከል አንዱ ናቸው::
አፍላ ጎረምሳ በነበርኩበት ዘመን ሁለት ጊዜ ማሰብና አዙሮ ማዬት የሚባለውን የህይወት ቁልፍ ነጥብ የተማርኩት ከእሳቸው ነው::
በአዘቦታዊ የኑሮ ዑደት ውስጥና በእኔ የስቪል ህይወት ውስጥ በእርጋታ አስቦ በአስተውሎት ለመወሰን የእሳቸው ተምሳሌት ቀላል አልነበረም::

በፈታኝ ወቅቶች ያለማወላወል...የአስቸኳይ እርምጃና የቁርጠኛ ውሳኔ አስፈላጊነትን በእርሳቸው ወታደራዊ አመራርና ድልአድራጊ አዋጊነት በፀጥታ ተምሬያለሁ::
ከዕዝና አስተዳደራዊ ተፅዕኗቸው ውጭ ካለው ማህበረሰብ ጋር በተግባቦት ለመኖር ይፈጥሩት የነበረው የሠላማዊ ወንድማማችነት የአኗኗር ስልት ዛሬም አብነቱ ህያው ሆኖ አብሮኝ ይኖራል::
ለእኔ ብርጋዴር ጄነራል ለገሠ አበጄን ያህል ታላቅ ሰው ማወቅ.....ስለእሳቸው መናገርና ዕማኝ መሆን መቻል ልዩ ክብርን ይሰጠኛል:: በግዙፍ ዋርካ ስር የመጠለል አይነት ምቾትም ይሰማኛል::

ለሀገር ክብር ለታሪክና የወገን ፍቅር ሲባል በጠላት ፊት ከመንበርከክ ይልቅ እንደታላላቆቹ የሀገራችን ባለታሪኮች ሁሉ ሽጉጣቸውን የጠጡት ብርጋዴር ጄነራል ለገሠ አበጄ ለኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ህይወታቸውን የከፈሉልን ህያው ባለውለታችን ናቸው:: ገድልና ታሪካቸውም በኢትዮጵያውያን የተጋድሎ ታሪክ ውስጥ ህያው ሆኖ ይኖራል!!
ነፍስ ይማርልን‼️

Address

Addis Ababa
251

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when R.I.P posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share