Hawariyat Primary Hospital/የሀዋርያት መጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • Hawariyat Primary Hospital/የሀዋርያት መጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል

Hawariyat Primary Hospital/የሀዋርያት መጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል Quality and Equitable Health Service for All .
ጥራት ያለው፤ፍትሀዊ የሆነ የጤና አገልግሎት ለሁሉም።

የሁሉም ትብብር እና ድጋፍ በውጤት ሲታጀብ.. የሐዋርያት መጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ ከጀመረበት 26/04/16 ከምንም የላብራቶሪ  ጥራት ደረጃ በ2017 የክልሉ ጤና ቢሮ የላብራቶሪ ጥራት ...
01/08/2026

የሁሉም ትብብር እና ድጋፍ በውጤት ሲታጀብ..

የሐዋርያት መጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ ከጀመረበት 26/04/16 ከምንም የላብራቶሪ ጥራት ደረጃ በ2017 የክልሉ ጤና ቢሮ የላብራቶሪ ጥራት ስታንዳርድ(ደረጃ መለኪያ) መስፈርት ከደረጃ 2 ወደ በ2018 የላብራቶሪ ደረጃ ጥራት ማረጋገጫ መስፈርት(ሰታንዳርድ) ደረጃ 4(አራት) መሸጋገር የሁሉም አስተዋፅኦ እና ድጋፍ ላቅ ያለ ነው። ባጭር ጊዜ ውስጥ ለዚህ ደረጃ መድረስ የተባበራችሁ፤የበኩላችሁን አስተዋፅኦ ላደረጋችሁ በማህበረሰቡ ስም ምስጋና ይገባችኋል። ቀጣይ የላብራቶሪ ጥራት ደረጃ ማረጋገጫ እና የ ደረጃ 5 እና Accrediation እውቅና ለማግኘት የሁሉም ትብብርና ድጋፍ ይሻል።

የሀዋሪያት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በተሟላ ግብዓት ለማህበረሰቡ ዘላቂ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ለማድረግ ቦርዱ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በትኩረት እየሰራ ነው፦አቶ አ...
31/07/2026

የሀዋሪያት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በተሟላ ግብዓት ለማህበረሰቡ ዘላቂ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ለማድረግ ቦርዱ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በትኩረት እየሰራ ነው፦አቶ አበራ ወንድሙ

ሐምሌ 24/2018ዓ.ም (ምሁር አክሊል ሐዋርያት)

የሀዋሪያት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ተግባራት እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ላይ ያተኮረ የቦርድ አባላት የውይይት መድረክ አካሂደዋል።

የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምርያ ዋና ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ የሀዋሪያት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በተሟላ ግብዓት ለማህበረሰቡ ዘላቂ አገልግሎት መስጠት እንዲችል ለማድረግ ቦርዱ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በትኩረት እየሰራ ነው።

የህዝባችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ሆስፒታሉ በሙሉ አቅሙ ጥራት ያለውና ተደራሽ የሆነ አገልግሎት መስጠት እንዲችል አስፈላጊውን የሆኑ ጉዳዮች ቅድሚያ በመሰጠት መስራት ያስፈልጋል።

ቅንጅታዊ አሰራር ይበልጥ በማጠናከር በሆስፒታሉ ውስጥ ሊያጋጥሙ ሚችሉ ችግሮች ደረጃ በደረጃ በመፍታት ውጤታማ ስራዎች ለመስራት ከማህበረሰቡ ጋር ተቀራርቦ ሊሰራ እንደሚገባም ጠቁመዋል።

ሆስፒታሉ ለማህበረሰቡ የተሟላ አገልግሎት መስጠት እንዲችል የህክምና ቁሳቁሶች እና ሌሎችም ተያያዥነት ባለቸው ጉዳዮች ከሚመለከታቸው አካል ጋር በመሆን ደረጃ በደረጃ ለመፍታት እንደሚሰራም ተናግረዋል።

የጉራጌ ዞን የጤና መምሪያ ዋና ኃላፊ አቶ አየለ ፈቀደ እንደገለፁት የሐዋርያት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለማህበረሰቡ ተገቢውን አገልግሎት እየሰጠ እንደነበርና በዚህም አላስፈላጊ እንግልትን ለመቀነስ የህክምና መሳርያዎች ለማሟላት የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።

ሆስፒታሉ በተሟላ ግብዓት የተሟላ አገልግሎት ለማህበረሰቡ ለመስጠት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን የተለያዩ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቁመው በቀጣይ ለተቋሙ አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶች እንዲሟሉ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል።

ሆስፒታሉ በበጀት ዓመቱ በርካታ ተግባራት ማከናወኑንና ተጨባጭ ውጤት እየተመዘገበ መምጣቱ የምሁር አክሊል ወረዳው ዋና አስተዳደር አቶ ብስራት ገብሩ ተናግረዋል።

ውይይቱ የበጀት ዓመቱ የተግባር አፈፃፀም በመገምገም ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች በመለየት ለቀጣይ ስራዎች የሚያግዙ አቅጣጫዎች ለማስቀመጥ መሆኑን አመላክተዋል።

ሆስፒታሉ ለማህበረሰቡ ተገቢውን አገልግሎት በተሟላ ግብዓት ለመስጠት ከዞን፣ ከክልልና ከአካባቢ ተወላጅ ጋር እንዲሁም ከወረዳው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቁመው በ2019በጀት ዓመት የተሟላ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ስራ እየተሰራ ይገኛል።

የህክምና ቁሳቁሶች እንዲሟሉ የሚደረገው ጥረት በማጠናከር ማህበረሰቡ የሚፈልገውንና ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኝ ማድረግ የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች መሆናቸውን አቶ ብስራት ተናግረዋል።

በውይይቱ በበጀት ዓመቱ በሆስፒታሉ የተከናወኑ ተግባራትና በስራ ላይ ማነቆ የሆኑ ችግሮች መነሻ ሪፓርት በሆስፒታሉ ስራ- አስኪያጅ አቶ አበራ ውድማ ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።

ሆስፒታሉ በወረዳ ላሉ 30 ቀበሌዎች፣ ለ5 ጤና ጣቢያዎች፣ በስሩ ለሚገኙ ሦስት ጤና ኬላዎች በጥቅሉ ለወረዳው ማህበረሰብ እና ለአጎራባች ወረዳዎች አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ስራ_አስኪያጁ ገልፀዋል።

የህክምና መሳርያዎች ጉድለት በመኖሩ እና አማራጭ የሀይል ምንጭ አለመኖር ምክንያት ወሊድ፣ ጀነኔተር፣ የደም ፍሪጅ፣ ያልተሟሉ የቀዶ ህክምና መስጫ መሳሪያዎች፣ ድንገተኛ ህመሞች፣ የጨቅላ ህፃናት ህክምና እና የላብራቶሪ አገልግሎት መቆራረጥ የሚያጋጥሙ መሆኑን ጠቅሰው ክልሉ፣ የዞኑ ጤና መምሪያና ሌሎችም አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ መልእክት አስተላልፈዋል።

በመጨረሻም የ2019በጀት ዓመት እቅድ በቦርዱ የጋራ ተደርጓል ሲል የዘገበው የምሁር አክሊል ወረዳ የመንግስት ኮምዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ነው።

20/02/2026
20/02/2026
ፍፁም ስህተት፤ተጨባጭነት የሌለው ፤የተቋምን ስም ለማጠልሸት የተሰራጨ የተሳሳተ ወሬ‼️የሀዋርያት የመጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል ከተቋቋመ 2አመት ጊዜ ጀሞሮ በወረዳው መንግስት ሰፊ ጥረት፤በማህበረ...
20/02/2026

ፍፁም ስህተት፤ተጨባጭነት የሌለው ፤የተቋምን ስም ለማጠልሸት የተሰራጨ የተሳሳተ ወሬ‼️
የሀዋርያት የመጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል ከተቋቋመ 2አመት ጊዜ ጀሞሮ በወረዳው መንግስት ሰፊ ጥረት፤በማህበረሰብ ትብብር እና በሌሎች አጋሮች ጋር በመሆን የሆስፒታሉ አገልግሎት ከጊዜ ወደ ወደ ጊዜ በማስፋት እና አገልግሎቶችም ለማስፋፋት ከሚመለከታቸው በየደረጃው ከሚገኙ ከመንግስት አና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር አቅዶ እየሰራ የገኛል። ሆስፒታሉ ስራ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የእናቶች እና የጨቅላ ህፃናት እንዲሁም ብዙ ሰዎች ለእንግልት እና ለሞት ሳይዳረጉ በመንግስት እና በማህበረሰብ ትብብር በተገዙ የህክምና መገልገያ መሳርያዎች የበርካቶችን ህይወት ታድጓል። ነገር ግን የፖለቲካል ትርፍ ለማግኘት ሲባል የተቋሙን ስም ማጠልሸት ተገቢ እንዳልሆነ እና ግለሰቦች ከዚህ ድርጊታቸው ሊታረሙ ይገባል። ሞት በተቋም/ከተቋም ውጪ በብዙ ምክንያቶች ሊከሰት ይችላል፤ቢኖርም ሆስፒታሉ የሚደብቀው መረጃ አይኖርም። ነገር ግን ይህ በዳንኤል ተረፈ በሚል የማህበራዊ ድህረ ገፅ ላይ የተሰራጨው መረጃ ሆስፒታሉን የማይገልፅ ፣ሆስፒታሉ ስራ ከጀመረ ጀምሮ አንድም የወላድ እናት ሞት በሆስፒታሉ ያለተከሰተ እና ሆስፒታሉን የማይወክል መሆኑን ማህበረሰባችን እና ተገልጋዮቻችን ግንዛቤ እንዲኖራቸው እናሳውቃለን።

የሀዋርያት የመጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል

የሐዋርያት የመጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 አ.ም የ2ተኛ ሩብ አመት የቦርድ ውይይት አደረገ።በውይይቱ  የሆስፒታሉ ቦርድ ዋና  ሰብሳቢ ፣የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና መም...
14/02/2026

የሐዋርያት የመጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 አ.ም የ2ተኛ ሩብ አመት የቦርድ ውይይት አደረገ።
በውይይቱ የሆስፒታሉ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ፣የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ እና የግብርና መምሪያ ሀላፊ የተከበሩ አቶ አበራ ወንድሙ ፤የሆስፒታሉ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ እና የምሁር አክሊል ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ የተከበሩ አቶ ብስራት ገብሩ ፤ የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ ሀላፊ አቶ አየለ ፈቀደ እና ሌሎችም የቦርድ አባላት ተገኝተዋል ።
የግማሽ አመቱ አፈፃፀም በሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ በአቶ አበራ ውድማ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። በመድረኩም ከባለፈው ውይይት የተቀመጡ አቅጣጫዎች አፈፃፀም፤የቁልፍ አመላካች ፤የዋና ዋና ተግባራት እና የፋይናንስ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጓል።
ከባለፈው ውይይት በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በሀብት አሰባሰቡ ንቅናቄ በተገኘው ገንዘብ በሆስፒታሉ ወሳኝ የሆኑ የአገልግሎት ስራ ክፍሎች በተለይም የቀዶ ጥገና ህክምና ክፍል ማደራጀት እና አገልግሎት ማስጀመር፣የአልትራ ሳውንድ፤የራጅ አገልግሎት እና በላብራቶሪ ክፍል ከዚህ ቀደም ያልተጀመሩ ምርመራዎች ፤የእናቶች እና የጨቅላ ህፃናት ህክምና ክፍል እና ሌሎች አገልግሎቶች የሚያጠናክሩ የህክምና መገልገያ መሳርያዎች በግማሽ አመቱ ከስምንት ሚሊየን ብር በላይ በፈጀ ወጪ በተሰበሰበው ሀብት ግዢ ተፈፅሞ አገልግሎት የማስጀመር ስራ መሰራቱን በቀረበው ሪፖርት ተመላክቷል።
በውይይቱ የሆስፒታሉ አገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደጊዜ መሻሻሉ እና የተጀመረውን መልካም ጅማሮ ማስቀጠል እና የሚስተዋሉ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮች በጊዜ ተከታትሎ መፍታት እና ለማህበረሰቡ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባም ተመላክቷል።
የተጀመሩ አገልግሎቶች ማጠናከር፣ማስፋፋት እና ያልተጀመሩ የህክምና አገልግሎት ክፍሎች ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር ፤ የተጀመረው የሀብት አሰባሰብ በማጠናከር መስራት እንደሚገባ እና ለማህበረሰቡ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት እንደሚገባ የሆስፒታሉ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ አቶ አበራ ወንድሙ ገልፀዋል።
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ እና የሆስፒታሉ ቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ብስራት ገብሩ እንደገለፁት በቀጣይ የሆስፒታሉ ሙሉ የስራ ክፍሎች የሚያንቀሳቅስ ዘላቂ እና ተተኪ የሀይል አማራጭ (ሶላር ወይም ጀነሬተር) እና የደም ማስቀመጫ ፍሪጅ እንዲሁም ሌሎች አስፈላጊ የህክምና መገልገያ መሳርያዎች ጉድለት የማሟላት ስራ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ታቅዶ በቅንጅት እንደሚሰራ ገልፀዋል። ዋና አስተዳዳሪው አክለውም ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት ያለምንም እንግልት ለማህበረሰቡ መስጠት እንደሚገባ እና የተጀመሩ ጅማሮዎች ማጠናከር እንደሚገባ አሳስበዋል።በመጨረሻም የሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር በመወከል ተጠናቋል።

በጎ ተግባር ፤ሕይወትን ለመታደግ። በሐዋርያ መጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል ። 03/06/2018 ዓ.ም
10/02/2026

በጎ ተግባር ፤ሕይወትን ለመታደግ። በሐዋርያ መጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል ። 03/06/2018 ዓ.ም

Address

Hawariyat
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Hawariyat Primary Hospital/የሀዋርያት መጀመርያ ደረጃ ሆስፒታል posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category