20/05/2026
እኛ የዳንግላ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎች የ 6 ወር ዱዩቲያችን በጉልበተኞች ተነጥቀናል : ፍርድ ቤት ክስ ጀምረናል ። የኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሆይ?, የክልል ጤና ቢሮ ሀላፊዎች ሆይ! በያላችሁበት ይሰማል ወይ ? "ከልጆቻችን አፍ ላይ ዳቦ ቀምታችሁ እንደበላችሁባቸው ነው የምንቆጥረው! !
የዳኛ ያለህ? የፍትህ ያለህ? የመንግስት ያለህ? የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልን! ! በየጤና ሴክተሩ በየቢሮው የተኮለኮሉ ጉልበተኛ ወጠጤዎች የድካማችንን ክፍያ በቀን በጠራራ ፀሐይ ቀሙን! ! እንደድሮው ( በሀይለስላሴ አምላክ! አይባል ነገር ሀይለስላሴ ሙቷል ! !) በጠቅላይ ሚኒስቴሩ በአብይ አይመድ አምላክ ገንዘባችንን መልሱ! እኛንና ህጉን ባትፈሩ የላይኛውን ባለቤቱን ፍሩት ። ምን ጉድ ነው? እንዴ ነውር አይደለም እንዴ? ጤና ባለሙያው የላቡ የድካሙ ውጤት ሊከፈለው አይገባም ወይ? ? ኧረ ወገን ፍረዱን ተበላን!! ከላይ ፈጣሪ ከታች የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረደን !! የጣሊያን የሲሲሊ ማፍያዎች እኮ ቢዘርፉም ወንበዴ መሆናቸውን በይፋ አሳውቀው ነው! ! እኛ እንዴት በማንም ጎረምሳ የትርፍ ሰዓት አዳር ክፍያችን ይነጠቃል? ? ነውር ;የነውርም ነውር ነው!! ግፍ! የግፍ ግፍ ነው!! እንዴ? በቃ አዳር ፕሮግራም ይቅር የለም ከተባለ እስካሁን የደከምንበትን ክፈሉና ከዚህ በሗላ ቀን ሰርተን ማታ ከቤታችን ከልጆቻችን ጋር እንደር ። ያልሰራንበት አያምረንም! ቁርጣችን አውቀን እንቀመጣለን ። ስራ ካሰሩ በሗላ ክፍያ መከልከል ግን በምድራዊ ህግም በፈጣሪም ዘንድ ያስጠይቃል !! ለሚሰማ ሁሉ እርግጠኛ ሁኜ የምነግራችሁ ለእናንተ የማይገባችሁን ጥቅምና የሰው የድካም ውጤት እናንተው ያለልክ በውሎ አበል መልክ ብትበሉት ደም ግፊት, ስኳር, ልብ ድካም, ጨንጓራ ቁስለት, ኩላሊትና ጭንቀት ያመጣባችሗል !! እንቅልፍ ማጣት, ራስ ምታት, ኩላሊት ጠጠር, ጎን ውጋት, መገጣጠሚያ ቁርጥማት ይለቅባችሗል! ! አልሰማንም እንዳትሉ! ከዚህ ከተዘረዘሩት አንዱን አይነፍጋችሁም ። በሀገሪቱ 4ቱም አቅጣጫ ጤና ባለሙያው እየተንጫጫ ሰምተህ እንዳልሰማህ ጭጭ ያልክ ሁሉ ጎን ውጋት ሲይዝህ አስታወሰኝ! ብሎኝ ነበር , ነግሮኝ ነበር :ትላለህ እንጅ የዲዩቲውን በጀት ወደ ውሎ አበል ቀይራችሁ ብትቀረጥፉት ለእናንተ አይጠቅምም 100% ። አንድ ምስኪን ጤና ባለሙያ የ 6 ወር ዲዩቲ ክፍያ ተቀማ ማለት በትንሹ 60,000 ብር ተቀማ ማለት ነው, 60,000ብር ደግሞ የ 6 ኩንታል ጤፍ ዋጋ ነው! ! 6 ኩንታል ጤፍ ደግሞ የ3 አመት የልጆቻችን ቀለብ ተወሰደብን ማለትም አይደል? ይሄ ነገር እንዴት ነው? እንዴ? ኧረ ይሄ ነገር አይበጅም ተው እንደማመጥ? እስኪ በደንብ ሼር አርጉትና ሰው አስተያየቱንና መፍትሔውን ይስጥ?
ኢትዮጵያ እስከአለም ፍፃሜ ትኑር !! ጠላቶቿ ይነቀሉ ።