Digital Hakim

Digital  Hakim Physicians activist
(4)

21/05/2026

የደሞዝተኛው ግብር ፍትሀዊ አይደለም።
በዝቷል ይቀነስ!!
___
ቻሌንጁን ተቀላቀሉ!!

🚨 Vacancy Announcement 🚨
21/05/2026

🚨 Vacancy Announcement 🚨

የተሳሳተ መረጃ
21/05/2026

የተሳሳተ መረጃ

21/05/2026

እኛ በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ጥበበ ግዮን ሆስፒታል የምንገኝ ረዚደንት ሐኪሞች የመኖሪያ ዶርሚተሪ አትሰጡም ተባልን ።ምክንያቱ ደግሞ ትዳር መስርታችኋል:ልጅ ወልዳችኋል ህንጻው ይበላሻል ነው ።

እጥፍ ድርብ ኃላፊነት ያለብን ሐኪሞች መኖር አልቻልንም ።

ድምጽ ሁኑን።

20/05/2026

እኛ የአገው ግምጃቤት የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎች የ 6 ወር ዱዩቲያችን በጉልበተኞች ተነጥቀናል : ነገር ግን ባለሞያዎች አግባብ ባለ የዲውቲ ተጠቃሚዎች በሙሉ ይከፈለን ጥያቄ ሰንጠይቅ አላፊዎች እኛም መረጃ የለንም እንደናተው ነን ዝም ብላችሁ ስሩ ዛሬ 11/9/2018 ባለሞያ ሰብሰባ ጠርቶ አለበለዚያ ትታሰራላችሁ ተብለናል የኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሆይ?, የክልል ጤና ቢሮ ሀላፊዎች ሆይ! በያላችሁበት ይሰማል ወይ ? "ከልጆቻችን አፍ ላይ ዳቦ ቀምታችሁ እንደበላችሁባቸው ነው የምንቆጥረው! !
የዳኛ ያለህ? የፍትህ ያለህ? የመንግስት ያለህ? የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልን! ! በየጤና ሴክተሩ በየቢሮው የተኮለኮሉ ጉልበተኛ ወጠጤዎች የድካማችንን ክፍያ በቀን በጠራራ ፀሐይ ቀሙን! ! እንደድሮው ( በሀይለስላሴ አምላክ! አይባል ነገር ሀይለስላሴ ሙቷል ! !) በጠቅላይ ሚኒስቴሩ በአብይ አይመድ አምላክ ገንዘባችንን መልሱ! እኛንና ህጉን ባትፈሩ የላይኛውን ባለቤቱን ፍሩት ። ምን ጉድ ነው? እንዴ ነውር አይደለም እንዴ? ጤና ባለሙያው የላቡ የድካሙ ውጤት ሊከፈለው አይገባም ወይ? ? ኧረ ወገን ፍረዱን ተበላን!! ከላይ ፈጣሪ ከታች የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረደን !! የጣሊያን የሲሲሊ ማፍያዎች እኮ ቢዘርፉም ወንበዴ መሆናቸውን በይፋ አሳውቀው ነው! ! እኛ እንዴት በማንም ጎረምሳ የትርፍ ሰዓት አዳር ክፍያችን ይነጠቃል? ? ነውር ;የነውርም ነውር ነው!! ግፍ! የግፍ ግፍ ነው!! እንዴ? በቃ አዳር ፕሮግራም ይቅር የለም ከተባለ እስካሁን የደከምንበትን ክፈሉና ከዚህ በሗላ ቀን ሰርተን ማታ ከቤታችን ከልጆቻችን ጋር እንደር ። ያልሰራንበት አያምረንም! ቁርጣችን አውቀን እንቀመጣለን ። ስራ ካሰሩ በሗላ ክፍያ መከልከል ግን በምድራዊ ህግም በፈጣሪም ዘንድ ያስጠይቃል !! ለሚሰማ ሁሉ እርግጠኛ ሁኜ የምነግራችሁ ለእናንተ የማይገባችሁን ጥቅምና የሰው የድካም ውጤት እናንተው ያለልክ በውሎ አበል መልክ ብትበሉት ደም ግፊት, ስኳር, ልብ ድካም, ጨንጓራ ቁስለት, ኩላሊትና ጭንቀት ያመጣባችሗል !! እንቅልፍ ማጣት, ራስ ምታት, ኩላሊት ጠጠር, ጎን ውጋት, መገጣጠሚያ ቁርጥማት ይለቅባችሗል! ! አልሰማንም እንዳትሉ! ከዚህ ከተዘረዘሩት አንዱን አይነፍጋችሁም ። በሀገሪቱ 4ቱም አቅጣጫ ጤና ባለሙያው እየተንጫጫ ሰምተህ እንዳልሰማህ ጭጭ ያልክ ሁሉ ጎን ውጋት ሲይዝህ አስታወሰኝ!

20/05/2026

እኛ የዳንግላ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎች የ 6 ወር ዱዩቲያችን በጉልበተኞች ተነጥቀናል : ፍርድ ቤት ክስ ጀምረናል ። የኢትዮጵያ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሆይ?, የክልል ጤና ቢሮ ሀላፊዎች ሆይ! በያላችሁበት ይሰማል ወይ ? "ከልጆቻችን አፍ ላይ ዳቦ ቀምታችሁ እንደበላችሁባቸው ነው የምንቆጥረው! !
የዳኛ ያለህ? የፍትህ ያለህ? የመንግስት ያለህ? የኢትዮጵያ ህዝብ ይወቅልን! ! በየጤና ሴክተሩ በየቢሮው የተኮለኮሉ ጉልበተኛ ወጠጤዎች የድካማችንን ክፍያ በቀን በጠራራ ፀሐይ ቀሙን! ! እንደድሮው ( በሀይለስላሴ አምላክ! አይባል ነገር ሀይለስላሴ ሙቷል ! !) በጠቅላይ ሚኒስቴሩ በአብይ አይመድ አምላክ ገንዘባችንን መልሱ! እኛንና ህጉን ባትፈሩ የላይኛውን ባለቤቱን ፍሩት ። ምን ጉድ ነው? እንዴ ነውር አይደለም እንዴ? ጤና ባለሙያው የላቡ የድካሙ ውጤት ሊከፈለው አይገባም ወይ? ? ኧረ ወገን ፍረዱን ተበላን!! ከላይ ፈጣሪ ከታች የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረደን !! የጣሊያን የሲሲሊ ማፍያዎች እኮ ቢዘርፉም ወንበዴ መሆናቸውን በይፋ አሳውቀው ነው! ! እኛ እንዴት በማንም ጎረምሳ የትርፍ ሰዓት አዳር ክፍያችን ይነጠቃል? ? ነውር ;የነውርም ነውር ነው!! ግፍ! የግፍ ግፍ ነው!! እንዴ? በቃ አዳር ፕሮግራም ይቅር የለም ከተባለ እስካሁን የደከምንበትን ክፈሉና ከዚህ በሗላ ቀን ሰርተን ማታ ከቤታችን ከልጆቻችን ጋር እንደር ። ያልሰራንበት አያምረንም! ቁርጣችን አውቀን እንቀመጣለን ። ስራ ካሰሩ በሗላ ክፍያ መከልከል ግን በምድራዊ ህግም በፈጣሪም ዘንድ ያስጠይቃል !! ለሚሰማ ሁሉ እርግጠኛ ሁኜ የምነግራችሁ ለእናንተ የማይገባችሁን ጥቅምና የሰው የድካም ውጤት እናንተው ያለልክ በውሎ አበል መልክ ብትበሉት ደም ግፊት, ስኳር, ልብ ድካም, ጨንጓራ ቁስለት, ኩላሊትና ጭንቀት ያመጣባችሗል !! እንቅልፍ ማጣት, ራስ ምታት, ኩላሊት ጠጠር, ጎን ውጋት, መገጣጠሚያ ቁርጥማት ይለቅባችሗል! ! አልሰማንም እንዳትሉ! ከዚህ ከተዘረዘሩት አንዱን አይነፍጋችሁም ። በሀገሪቱ 4ቱም አቅጣጫ ጤና ባለሙያው እየተንጫጫ ሰምተህ እንዳልሰማህ ጭጭ ያልክ ሁሉ ጎን ውጋት ሲይዝህ አስታወሰኝ! ብሎኝ ነበር , ነግሮኝ ነበር :ትላለህ እንጅ የዲዩቲውን በጀት ወደ ውሎ አበል ቀይራችሁ ብትቀረጥፉት ለእናንተ አይጠቅምም 100% ። አንድ ምስኪን ጤና ባለሙያ የ 6 ወር ዲዩቲ ክፍያ ተቀማ ማለት በትንሹ 60,000 ብር ተቀማ ማለት ነው, 60,000ብር ደግሞ የ 6 ኩንታል ጤፍ ዋጋ ነው! ! 6 ኩንታል ጤፍ ደግሞ የ3 አመት የልጆቻችን ቀለብ ተወሰደብን ማለትም አይደል? ይሄ ነገር እንዴት ነው? እንዴ? ኧረ ይሄ ነገር አይበጅም ተው እንደማመጥ? እስኪ በደንብ ሼር አርጉትና ሰው አስተያየቱንና መፍትሔውን ይስጥ?
ኢትዮጵያ እስከአለም ፍፃሜ ትኑር !! ጠላቶቿ ይነቀሉ ።

First batch  obstetrics and gynecology graduates of Yirgalem Hospital Medical College 2026GC. .Yassin M. .Diba W. .Dagma...
20/05/2026

First batch obstetrics and gynecology graduates of Yirgalem Hospital Medical College 2026GC.
.Yassin M.
.Diba W.
.Dagmawi M.
.Baye S.

19/05/2026

እኛ በደቡብ ጎንደር ዞን የፋርጣ ወረዳ የጤና ባለሙያዎች የስድስት (6) ወር የዲዩቲ ክፍያ ያልተከፈለን በመሆኑ የሚመለከተውን አካል በተደጋጋሚ ብንጠይቅም ምላሽ የሚሰጥን በማጣታችን ጉዳዩን በህግ አግባብ ተይዞ ጉዳዩን እየተከታተልን ነው፡፡ ነገር ግን በወረዳ ጽ/ቤት ሀላፊው እና በወረዳ አስተዳዳሪ አማካኝነት በባለሙያው እና የጤና ጣቢያ በሀላፊዎችና የባለሙያውን መብት ተወክለው በህግ በሚከታተሉ ባለሙያዎች ላይ በተለያዩ መድረኮች እንዲሁም በተናጠል ለማደርስባችሁ በቀል እና ለተለያዩ ጉዳት ተዘጋጁ እንተያያለን እየተባልን ሰው የሰራበትን ካልቃመሁ በሚል ስውር አስተሳሰብ በነውረኛ በተራ አማረኛ እየተዘለፍን ነው ፡፡ ለሀሉም ግፍን እና ብልሹ አሰራርን ለሚፀየፍ ሁሉ ድምፅ እንዲሆኑን አድርስልን?????

ህልመኛዋ ነርስ ሂንሴኔ ተፈሪ የገዛ ሕይወቷን አጠፋች!😭 ወጣቷ ሂንሴኔ ተፈሪ ፤ "ነርስ ሆኜ የሰዎችን ህይወት እታደጋለሁ" የሚል ትልቅ ህልም ነበራት። ለ4 ዓመታት ቀን ከሌሊት ደክማለች። በ...
18/05/2026

ህልመኛዋ ነርስ ሂንሴኔ ተፈሪ የገዛ ሕይወቷን አጠፋች!😭

ወጣቷ ሂንሴኔ ተፈሪ ፤ "ነርስ ሆኜ የሰዎችን ህይወት እታደጋለሁ" የሚል ትልቅ ህልም ነበራት። ለ4 ዓመታት ቀን ከሌሊት ደክማለች። በነቀምቴ ከተማ በሚገኘው የኒው ጀነሬሽን ኮሌጅ የ4ኛ ዓመት የቢኤስሲ ነርሲንግ (BSc Nursing) ተማሪ የነበረችው ሂንሴኔ ተፈሪ፣ በትምህርቷ ጎበዝ፣ በትጋቷ በጓደኞቿ ዘንድ የምትወደድና ነገ ትልቅ ደረጃ ትደርሳለች ተብሎ ተስፋ የተጣለባት ወጣት ነበረች።

ነገር ግን ፤ ያ ሁሉ የዓመታት ልፋቷና ያማረ ህልሟ በአንድ ጀምበር ጨለመ። ለብዙ ዓመታት ለፍታ እዚህ የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ የደረሰችው ሂንሴኔ፣ የኮሌጁን የ15,000 (አስራ አምስት ሺህ) ብር የትምህርት ክፍያ መክፈል አልቻለችም።

በዚህም ምክንያት ለዓመታት የደከመችበትን ሀገር አቀፍ የብቃት መመዘኛ (Exit Exam) መፈተን እንደማትችል በኮሌጁ ይነገራታል። ያሳለፈችውን ውጣ ውረድ የምታውቀው ሂንሴኔ፣ በብር ምክንያት ህልሟ ሲቀጭባት መቋቋም አልቻለችም። ጓደኞቿ በሙሉ ወደ ፈተና አዳራሽ ሲገቡ፣ እሷ ግን በገንዘብ እጥረት ምክንያት ብቻ ወደ ኋላ ቀረች።

ይህ ብቸኝነት፣ የደረሰባት ከባድ የሥነ-ልቦና ጫና እና የተስፋ መቁረጥ ስሜት ወደ ከፋ ውሳኔ መራት ፤ የገዛ ሕይወቷን አጠፋች። ታሪኳ ሲሰማ ልብ ይሰብራል፣ ሕሊናንም ያደማል።

በብርሃን ፍጥነት ተመርቃ፣ ነጭ ጋውን ለብሳ የሰዎችን ሕይወት ልትታደግ የነበረችው ውዷ እህታችን፣ ዛሬ በ15 ሺህ ብር ምክንያት ሕይወቷ እንዲህ መቅጠፉ እጅግ ያማል! እጅግ ያበሳጫል!

ይህ አሳዛኝ ክስተት ለአንድ ማህበረሰብ ትልቅ የቤት ሥራና የህሊና ጥያቄ ነው። ዛሬ ስንት ሂንሴኔዎች በውስጣቸው እየተቃጠሉ፣ የሚረዳቸው አጥተው በተስፋ መቁረጥ ውስጥ ይኖሩ ይሆን?! ለሂንሴኔ ተፈሪ ቤተሰቦች፣ ለጓደኞቿና ለወዳጆቿ በሙሉ ፈጣሪ መጽናናቱን ይስጥ።

ማለዳ መረጃ - Maleda Merja

የእግዚአብሔር ሐሳብ~~~~~~~~~~~      # # # በዚህ ባለንበት ዘመን ዕለት ዕለት በሚደረገው እንቅስቃሴ በአብዛኛው ሰዎች ላይ የምናስተውለው ባህሪ አሳሳቢ ነው ::  ሰዎች ራሳቸውን ...
18/05/2026

የእግዚአብሔር ሐሳብ
~~~~~~~~~~~

# # # በዚህ ባለንበት ዘመን ዕለት ዕለት በሚደረገው እንቅስቃሴ በአብዛኛው ሰዎች ላይ የምናስተውለው ባህሪ አሳሳቢ ነው :: ሰዎች ራሳቸውን የሚወዱ ፥ ገንዘብን የሚወዱ፥ ትምክህተኞች፥ ትዕቢተኞች፥ ተሳዳቢዎች፥ ለወላጆቻቸው የማይታዘዙ፥ የማያመሰግኑ፥ቅድስና የሌላቸው፥ ፍቅር የሌላቸው፥ ዕርቅን የማይሰሙ፥ ሐሜተኞች፥ ራሳቸውን የማይገዙ፥ ጨካኞች፥ መልካም የሆነውን የማይወዱ፥ከዳተኞች፥ ችኩሎች፥ በትዕቢት የተነፉ፥ ከእግዚአብሔር ይልቅ ተድላን የሚወዱ : የሃይማኖት መልክ ያላቸው አስመሳዬች ሁነው እናያለን:: ብዙዎቻችን ደግሞ እንደመሰለን ምክንያታዊ ለመሆን እና የችግሩን መንስኤ ለማስረዳት እንሞክራለን :: ምክንያቱ ግን ከእግዚአብሔር ሐሳብ ርቀን በራሳችን ሐሳብ መመራታችን ነው ( 2ኛ ጢሞ 3÷ 1 - 5 ምሳ 3÷ 7)

# # # የእግዚአብሔር ሐሳብ ሰው ሁሉ ዳግም (ለሁለተኛ ግዜ) እንዲወለድ እና አዲስ ፍጥረት እንዲሆን ነው:: ሰው ሁሉ ዳግም መወለድ የሚችለው ደግሞ በፍጹም ነፍሱ: በፍጹም ልቡ : በፍጹም ኃይሉ ጌታችን መድሀኒታች ኢየሱስ ክርስቶስን ሲያምን እና ሲወደው ብቻ ነው:: ከዚህም የተነሳ እርሱን ወደ መምሰል ይለወጣል:: የእርሱን ባህሪም ይላበሳል:: ( 2ኛ ቆሮ 5÷17 ; ሮሜ 8÷29) ስለዚህም መፍትሄው ዳግም መወለድ እና አዲስ ፍጥረት መሆን ብቻ ነው::

# # # ከሰው ሐሳብ ይልቅ እጅግ የላቀ የእግዚአብሔር ሐሳብ ለችግሮቻችን ሁሉ የመፍትሄ ሐሳብ ነው::

ወስብሃት ለእግዚአብሔር

Dr Amsalu Bitew Internist , Pulmonologist

በየዓመቱ ረዚደንት ከመለመን ምንድ ነው ችግሩ ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው CC :MOH
16/05/2026

በየዓመቱ ረዚደንት ከመለመን ምንድ ነው ችግሩ ብሎ መጠየቅ ተገቢ ነው
CC :MOH

Address

Kazanchis
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Digital Hakim posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category