Arbaminch General Hospital

Arbaminch General Hospital ይህ የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ትክክለኛው የፌስቡክ ገጽ ነው!

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የፓንደሚክ ፈንድ የቦርድ ተባባሪ ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ__________የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የፓንደሚክ ፈንድ የበላይ ቦርድ ተባባሪ ሊቀመንበ...
19/06/2026

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የፓንደሚክ ፈንድ የቦርድ ተባባሪ ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ
__________

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የፓንደሚክ ፈንድ የበላይ ቦርድ ተባባሪ ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።

የፓንደሚክ ፈንድ ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸዉ አገራትን አቅም በመገንባት ድንገተኛ የጤና አደጋ ክስተቶችን ለመከላከል፣ ለመለየትና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተቋቋመ መሊቲላተራል ፋይናንሲንግ አሰራር ሲሆን ሚኒስትሯ በአዲሱ ኃላፊነታቸው ዓለም አቀፍ አጋርነቶች እንዲጠናክር እና አገራት ወረርሽኞችን ለመከላከል ለሚያደርጉት ኢንቨስትመንት የሚሰጠውን ድጋፍ በበላይነት በመምራት ለዉጥ እንደሚያመጡ ፈንዱ ያለዉን እምነት ገልጸዋል፡፡

ዶ/ር መቅደስ ኃላፊነቱን የተረከቡት ከሩዋንዳ ጤና ሚኒስትር ከሆኑት ከዶ/ር ሳቢን ንሳንዚማና ሲሆን፣ ሚኒስትሯ ባስተላለፉት መልዕክት የህብረተሰባችንን ህይወት መታደግ የሚችልና የዓለምን የጤና ደህንነት ዋስትናን የሚያረጋግጥ ጠንካራ የጤና ስርዓት በመገንባት ለትዉልድ ማስተላለፍ አለብን ብለዋል።

Minister of Health Dr. Mekdes Daba elected as Co-Chair of the Pandemic Fund Board
____________

Minister of Health Dr. Mekdes Daba has been elected as a Co-Chair of the Pandemic Fund Governing Board.

The Pandemic Fund is a multilateral financing mechanism established by the global community to help build capacity in low- and middle-income countries to prevent, detect, and respond rapidly to public health emergencies. The Fund expressed its confidence that, in her new role, the Minister will bring about change by overseeing the strengthening of international partnerships and the support provided for investments made by countries to prevent pandemics.

Dr. Mekdes took over the responsibility from Dr. Sabin Nsanzimana, the Minister of Health of Rwanda. In her message, the Minister stated that we must build and pass on to future generations a strong health system that can save the lives of our society and ensure global health security.

ቋሚ ኮሚቴው በምግብ ስርዓት እና ስርዓተ-ምግብ ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ይፋዊ ውይይት አደረገ --------------(ዜና ፓርላማ) ሰኔ 8፣ 2018 ዓ.ም፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማ...
15/06/2026

ቋሚ ኮሚቴው በምግብ ስርዓት እና ስርዓተ-ምግብ ረቂቅ አዋጅ ዙሪያ ይፋዊ ውይይት አደረገ
--------------
(ዜና ፓርላማ) ሰኔ 8፣ 2018 ዓ.ም፣ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከጤና ሚኒስቴር፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እና ከሌሎች ተቋማት ጋር ረቂቅ አዋጁን በማስመልከት ይፋዊ የህዝብ ውይይት አድርጓል።

የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ወረቀሰሙ ማሞ ረቂቅ አዋጁ የአገራችን የምግብ ስርዓትንና የስርዓተ-ምግብ ሁኔታን ለማሻሻል ወሳኝ መሰረት እንዳለው ገልፀው፣አዋጆች የረጅም ጊዜ አገልግሎት እንዲሰጡ እና ዘመን ተሻጋሪ እንዲሆኑ የህዝብ አስተያየት ወሳኝ እንደሆነ እና ረቂቅ አዋጁ ትውልድ የሚገነባበት የምግብ ስርዓት ብቻ ሳይሆን ስርዓተ-ምግብንም አካቶ የተዘጋጀ መሆኑን ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት አገራችን በምግብ አቅርቦት፣ በስርዓተ-ምግብ ጥራት፣ በምግብ ደህንነት፣ በአየር ንብረት ለውጥ ተፅዕኖ፣ በምግብ ብክነት እና በዘርፎች መካከል በቂ ቅንጅት ለመፍጠር የሚያስችል ሥራዎችን መንግስት በከፍተኛ ትኩረት እየሰራ ቢሆንም በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን በዘላቂነት ለመፍታት የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት የተቋማትን ሚና እና ኃላፊነት በግልፅ መወሰን እንደሚያስፈልግው ሰብሳቢዋ አስረድተዋል።

በረቂቅ ውይይቱ ላይም መቀንጨርን ቀድመን ለመከላከል እናቶች ላይ የበለጠ ትኩረት ተሰጥቶት መካትተ እንዳለበትና የምግብ ስርዓት እና የስርዓተ-ምግብ የሚለው ስያሜ የኢትዮጵያ የምግብ ስርዓት የሚል ስያሜ እንዲሰጠው የመድረኩ ተሳታፊዎች አንስተዋል።

የጤና ሚኒስቴር ሚንስትር መቅደስ ዳባ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ በመድረኩ ላይ የተነሱ አስተያየቶችን እንደ ግብዓት ወስደው እንደሚሰሩ እና ረቂቅ አዋጁ በአገሪቱ በሁሉም አካባቢዎች እንደሚተገበርም አስገንዝበዋል።

ከተጠያቂነትና በጋራ ከመፈፀም አንፃር የተለያዩ ክፍተቶች ስለነበሩ ረቂቅ አዋጁ በዘላቂነት እና የጋራ አገር አቀፍ አዋጅ እንዲኖር ታስቦ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

ረቂቅ አዋጁ ነብሰ-ጡር እና ለሚያጠቡ እናቶችን ፣ ጨቅላ ህፃናትን ፣ አፍላ ወጣቶችን፣ አካል ጉደተኞችን፣ አረጋዊያን፣ በጤና ችግሮች ምክንያት በስርዓተ- ምግብና ህክምና ለሚያስፈልጋቸው ዜጎች፣ በተፈጥሮ ወይም በሰው ሰራሽ አደጋዎች ምክንያት በስርዓት- ምግብ መዛባት የተጋለጡ ዜጎች፣ ወላጆቻቸውን ያጡ ህፃናትን፣ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለባቸውን ዜጎች በልዩ ትኩረት ታሳቢ ያደረገና ትልቅ የትኩረት አቅጣጫ መሆኑን አብራርተዋል።

የጤና ሚኒስቴር ዴኤታ ከቡር ጀረጀ ዱጉማ (ዶ/ር) ረቂቅ አዋጁ ከመቀንጨር እና ከስርዓተ- ምግብ መዛባት ጋር የተያያዙ ችግሮች ከኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ እና አካባቢ ላይ የሚያስከትሉ ከፍተኛ አሉታዊ ተፅዕኖ ለማስቀረት እንደሚያግዝ አስረድተዋል።

ሚኒስትር ዴኤታው አክለውም አገራችን ፈርማ ያፀደቀቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን ተግባራዊ ለማድረግ የሕግ ማዕቀፍ በማስፈለጉ የምግብ ስርዓትን እና ስርዓተ- ምግብ ዘርፈ- ብዙ ቅንጅታዊ አሰራር የሚጠይቅ በመሆኑ ተጠያቂነት የሚያሰፍን አደረጃጀት አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።

የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ__________ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያ...
14/06/2026

የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ጤና ባለሙያዎች በሙሉ
__________

ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ ተመርቃችሁ የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባ ያጠናቀቃችሁ የጤና ባለሙያዎች በሙሉ፤ ፈተናው ከሰኔ 17 እስከ 19/2018 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን እየገለፅን፦

1. የፈተናው መርሃ-ግብርም፦
▪ በ17/10/2018 ዓ.ም…… Medicine, Public Health, Medical Laboratory Science, Midwifery, Medical Radiology Technology እና Pediatric and Child Health Nursing
▪ በ18/10/2018 ዓ.ም……, Nursing, Human Nutrition, Optometry, Physiotherapy እና Surgical Nursing
▪ በ19/10/2018 ዓ.ም…… Pharmacy, Anesthesia, Dental Medicine, Emergency and Critical Care Nursing, Environmental Health እና Psychiatric Nursing,

ሁሉም ተፈታኝ ሰኔ 16/2018 ዓ.ም ከሰዓት 8፡00 ሰዓት በመፈተኛ ጣቢያ በመገኘት ስለፈተናው አሰጣጥ ቅድመ ገለጻ (orientation) መከታተል፤ የቅድመ ፈተና መለማመጃ ጥያቄዎችን መስራትና፤ የመፈተኛ ክፍሉን መለየት ይኖርበታል::

2. በፈተናው ወቅት የብሄራዊ መታወቂያ (National ID) እንዲሁም ሲስተሙ የሚሰጠውን QR code ያለው የፈተና መግቢያ /ስሊፕ/ print out ይዛችሁ መገኘት ይኖርባችኋል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ እና Attachments የጤና ሚኒስቴ ቴሌግራም ቻናል ይመልከቱ፣ t.me/M0H_EThiopia

👉ወቅታዊ መረጃ ስለ  #ኢቦላ ከዞን ጤና መምሪያ በተላለፈልን መልዕክት መሠረት ለመላው ማህበረሰብ ክፍሉና ለጤና ባለሙያው የማንቂያና የቅድመ ጥንቃቄ ግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክት እንደሚከተለው ...
11/06/2026

👉ወቅታዊ መረጃ ስለ #ኢቦላ
ከዞን ጤና መምሪያ በተላለፈልን መልዕክት መሠረት ለመላው ማህበረሰብ ክፍሉና ለጤና ባለሙያው የማንቂያና የቅድመ ጥንቃቄ ግንዛቤ ማስጨበጫ መልዕክት እንደሚከተለው ቀርቧል።
በዓለም ጤና ድርጅት እይታ የዓለም ሕዝብ ጤና ችግር ሆኖ መከሰቱን በተለያዩ መንገዶች እንደተገለፀ ይታወቃል።
በሽታው መነሻ ያደረገው እና #በኡጋንዳ አካባቢ ከሚያዝያ ወር 2018 ዓም ጀምሮ የብዙ ሰው ሕመምና ሞት ምክንያት እየሆነ ይገኛል።በተለይ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የተለያዩ መረጃዎች እንደጠቆሙት እስከ እንደአውሮፓውያን አቆጣጠር ድረስ #344 ሰዎች መታመም እና #ከ60 በላይ ሰዎች ሞት የተረጋገጠ መሆኑ ሪፖርት ተተደርጓል።

በተያያዘም በሽታው ወደ ሌሎች አገሮች በፍጥነት ሊሰራጭ እንደሚችልም ተጠቁሟል።
የበሽታው አምጭው #ቫይረስ ሲሆን የተለያዩ ዝርያዎች እንዳሉትና በተለይ አሁን ላይ የሕዝብ ጤና ችግር ሆነው ሪፖርት የተደረጉት እና የተሰኙት እንደሆነ ተገልጻል።

የበሽታው አምጪ ተሸካሚዎች ደግሞ

#ዝንጆሮ
#ጉሬላ እና
#አጋዘን ዝርያዎች እንደሆኑ ተገልጿል።
ስለዚህም ከእነዚህ በሽታ ተሸካሚዎችና አምጪ እንስሳት ጋር የሚኖሩ ሰዎች ካሉ በሽታው በቀላሉ በንክኪ ይተላለፋል።

ሰዎች ለበሽታው ከተጋለጡ በኃላ ቀናት ውስስጥ ቀጥሎ የሚጠቀሱትን ምልክቶችን ማሳየት ይጀምራሉ
(ትኩሳት)
(ከባድ ራስምታት)
and (የጡንቻና የጉልበት ሕመም)
and Weakness(ፋታ አለመስጠትና ድካም)
and Diarrhea (ትውከትና ተቅማጥ)
Dysfunction and Manifestation (ደም የቀላቀለ ምልክቶች) ዋነኛ የበሽታው መገለጫው ነውና ይህን ምልክት በራሳቹ ላይ ሆነ በሌላ ግለሰብ ላይ ከተመለከታቹ በፍጥነት ወደ ሕክምና ተቋም እድትሄዱ ስንል ከወዲሁ በጥብቅ እናሳስባለን !!

🏥

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ  ተገኝተዉ የኢቦላ በሽታ ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያስችል የባለሙያች የተግባር ልምምድ (Simulation exercise) ...
07/06/2026

የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ በቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ተገኝተዉ የኢቦላ በሽታ ወረርሽኝን ለመከላከል የሚያስችል የባለሙያች የተግባር ልምምድ (Simulation exercise) ተመለከቱ፡፡
____________

የኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ ለመከላከል ዝግጁነት ለማጠናከር ይቻል ዘንድ በሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር የመግቢያና መውጫ የጤና ቁጥጥር ባለሙያዎች በቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ የጤና ልየታ፣ የቁጥጥር፣ የቅኝት ስራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ የባለሙያዎች ተግባራዊ ልምምድ Simulation exercise) የተመለከቱት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ ኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በዩጋንዳ አገራት ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከልን በማጠናከር ጥብቅ የሆነ የቅኝትና የልየታ ስራ እንዲሰራ የተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ወረርሽኞችንከመከላከልና ከመቆጣጣር አንጻር ከዚህ በፊት የነበሩትን ልምዶችና አሁን የተገኘውን እውቀት መሰረት በማድረግ በቀጣይ እስከ ታችኛው የጤና ተቋምና የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ቁጥጥር ባለሙያዎች በማውረድ ሁሉም ዝግጁ እንዲሆን ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን የገለጹት ሚኒስትሯ አገራችንን፣ ቤተሰባችንን፣ ሕብረተሰባችንን ከማንኛውም የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ችግሮች በመጠበቅና በመታደግ ለትውልድ የሚሻገር ስራ በመስራት ኃላፊነታችንን ልንወጣ ይገባል ብለዋል።

የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መሳይ ኃይሉ በበኩላቸዉ እንደገለጹት ኢቦላ ቫይረስ ወረርሽኝ በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ (DRC) እና በዩጋንዳ አገራት ከተከሰተ ጊዜ ጀምሮ የሕብረተሰብ ጤና አደጋ ማስተባበሪያ ማዕከልነ‍እ በማደራጀት በኢትዮጵያ ባሉ በአየርም ሆነ በየብስ በሚገኙ የመግቢያና መውጫ በሮች በኩል በሽታው ከተከሰተባቸው አገራት የሚመጡ ተጓዦችን የተላላፊ በሽታዎች ቁጥጥርና ቅኝት ስራዎችን ተጠናክረው እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

  !! ."  !!  🏥
06/06/2026

!!

.

" !!

🏥

ሁለተኛው የጤና ዘርፍ የመካከለኛ ዘመን የልማት እና ኢንቨስትመንት እቅድ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማትና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት...
05/06/2026

ሁለተኛው የጤና ዘርፍ የመካከለኛ ዘመን የልማት እና ኢንቨስትመንት እቅድ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማህበራዊ ልማትና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባላትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ውይይት ተካሄደ
_________

ቋሚ ኮሚቴው ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ብዙ ስራዎችን መስራት መቻሉን በውይይት መድረኩ ያስታወሱት የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ፤ ሁለተኛው የጤናው ዘርፍ የኢንቨስትመንት እቅድ ላይ ውይይት የሚያደርግበት መድረክ መሆኑን ተናግረዋል።

በሀገራችን አንድ እቅድ፣ አንድ በጀት እና ሪፖርት በመተግበሩ ዉጤት መገኘቱን ያነሱት ሚኒስትሯ፣ በተለይም በ2030 የተቀመጡ የጤና ልማት ግቦችን ለማሳካት አኢትዮጵያ በትክክለኛ መንገድ ላይ በመሆኗ ግባችንን ለመድረስ በትጋት የምንሰራበት ወቅት ነው ብለዋል። ባለፉት አመታት በእናቶችና ህጻናት ጤና፣ በሽታ መከላከል እና አክሞ ማዳን እና በወረርሽኝ ቅኝት እና ምላሽ አሰጣጥ የተገኙ ውጤቶችንም ገልጸዋል። የምክር ቤት አባላቱ ሙያዊ አስተዋጽኦዎቻቸውን እንዲያበረክቱ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ኮሚቴው እንደወትሮው ሁሉ ከጤና ሚ/ር ጋር በጋራ የሚሰራ መሆኑን ያነሱት የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ወ/ሮ ወርቀሰሙ ማሞ፣ የውይይት መድረኩ የተሰሩ ስራዎችን በመገምገም የቀረበው እቅድ ላይ ሃሳብ የሚቀርብበት መሆኑን ተናግረዋል።

የጤናው ዘርፍ ከሌሎች ባለድርሻ መስሪያ ቤቶች ጋር የሚሰሩ ስራዎችን በዝርዝር ያስቀመጠ እቅድ መሆኑን የገለጹት ወ/ሮ ወርቀሰሙ፣ የቀረበውን እቅድ የቋሚ ኮሚቴ አባላቱ በትኩረት በመመልከት በባለቤትነት ሀሳባቸውን እንዲያጋሩ አቅጣጫ ሰጥተዋል።

“ሰብአዊ ተግባር ሕይወት ይታደጋል፤ ብርሃን ይመልሳል” ሰኔ 07 — የዓለም የደምና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀንእንኳን ለዓለም የለጋሾች ቀን በሰላም አደረሳችሁ! ሰኔ 7 ቀን በበጎ ፈቃደኝነት ...
04/06/2026

“ሰብአዊ ተግባር ሕይወት ይታደጋል፤ ብርሃን ይመልሳል”
ሰኔ 07 — የዓለም የደምና የዓይን ብሌን ለጋሾች ቀን
እንኳን ለዓለም የለጋሾች ቀን በሰላም አደረሳችሁ!

ሰኔ 7 ቀን በበጎ ፈቃደኝነት ላይ ተመስርተው ክቡር ደማቸውን በመለገስ የሰውን ልጅ ሕይወት ለታደጉ እና የዓይን ብሌን ለመለገስ ቃል በመግባት ለወገኖቻቸው አዲስ ተስፋና የብርሃን ምንጭ ለሆኑ ውድ የሀገራችን በጎ ፈቃደኞች የላቀ ምስጋና የሚቀርብበትና ዕውቅና የሚሰጥበት ልዩ ዕለት ነው።

እያንዳንዱ የደም ልገሳ ውድ የሕይወት ማዳን ስጦታ ሲሆን፣ እያንዳንዱ የዓይን ብሌን ልገሳ ደግሞ ለሌላው ሰው ዓለምን በደመቀ ሁኔታ እንዲያይ የሚያደርግ ታላቅ ሰብአዊነት ነው። በአንድነት በመረባረብ ዘላቂ፣ አስተማማኝና ደህንነቱ የተጠበቀ የሕይወት አድን አቅርቦትን በሀገራችን ማረጋገጥ እንችላለን።

ዛሬውኑ ይወስኑ!
ደም በመለገስ ሕይወትን ይታደጉ፤ የዓይን ብሌን ለመለገስ ቃል በመግባት ብርሃን ይመልሱ!

በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ለፓርቲያቸው ያላቸውን አጋርነት ድምፃቸውን በመስጠት እንደሚያረጋግጡ ተናገሩአርባምንጭ፦ ግንቦት 19/2018 ዓ.ም (ጋሞ ...
27/05/2026

በአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ለፓርቲያቸው ያላቸውን አጋርነት ድምፃቸውን በመስጠት እንደሚያረጋግጡ ተናገሩ

አርባምንጭ፦ ግንቦት 19/2018 ዓ.ም (ጋሞ ዞን መ/ኮሙኒኬሽን)

የሆስፒታሉ የብልጽግና ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ይህን የተናገሩት የሆስፒታሉ የብልጽግና ፓርቲ ህብረት አመራሮች ባለፉት ወራት የተከናወኑ የህብረቱ ተግባራትን በተመለከተ ሪፖርት ለአባላቱ ባቀረቡበት መድረክ ላይ ነው።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የጋሞ ዞን ጤና መምሪያ ምክትል ኃላፊ ወ/ሮ ባንጌ ባንጃ ብልጽግና ፓርቲ በሁሉም ዘርፎች ሃገሪቱን ወደ ላቀ ደረጃ በማሻገር ላይ እንደሚገኝ ገልፀው ከእነዚህም የጤናው ዘርፍ አንዱ መሆኑን ጠቁመዋል።

በመሆኑም በ7ኛው ሃገራዊ ምርጫ በድምጽ መስጫ ዕለት የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ከቤተሰቦቻቸውና ጓደኞቻቸው ጋር በመውጣት ሃገሪቱን የብልጽግና ተምሳሌት ለማድረግ እየሰራ የሚገኘውን ብልጽግና ፓርቲ በመምረጥ አጋርነታቸውን እንዲያሳዩ ጥሪ አቅርበዋል።

የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር አምባቸው ዱማ በበኩላቸው በአርባምንጭ ሆስፒታል ከፍተኛ ቁጥር ያለው የብልጽግና ፓርቲ አባላት መኖራቸውን ጠቁመው ሁላችንም በድምፅ መስጫ ዕለት አጋርነታችንን በተግባር ማሳየት ይገባናል ብለዋል።

በተጨማሪም አባላቱና ደጋፊዎች በዕለቱ ደም በመለገስ ለህብረተሰቡ ያላቸውን አጋርነት በተግባር አሳይተዋል።

👉የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር አምባቸው ዱማ ለመላው የእስልምና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለ  #1447ኛው  (አረፋ) በዓል በሰላም በጤና አደረሳቹ ሲሉ መልካም ምኞታቸ...
27/05/2026

👉የአርባምንጭ አጠቃላይ ሆስፒታል ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር አምባቸው ዱማ ለመላው የእስልምና ዕምነት ተከታዮች እንኳን ለ #1447ኛው (አረፋ) በዓል በሰላም በጤና አደረሳቹ ሲሉ መልካም ምኞታቸውን ገለጹ።

በዓሉ #የሠላም, #የጤና, #የብልጽግና እንዲሆንላቹ ሲል መልካም ምኞቱን ይገልጻል 🙏


🏥

Address

Gamo Zone
Arba Minch'

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arbaminch General Hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share