19/06/2026
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የፓንደሚክ ፈንድ የቦርድ ተባባሪ ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ
__________
የጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የፓንደሚክ ፈንድ የበላይ ቦርድ ተባባሪ ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።
የፓንደሚክ ፈንድ ዝቅተኛና መካከለኛ ገቢ ያላቸዉ አገራትን አቅም በመገንባት ድንገተኛ የጤና አደጋ ክስተቶችን ለመከላከል፣ ለመለየትና ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እንዲቻል በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተቋቋመ መሊቲላተራል ፋይናንሲንግ አሰራር ሲሆን ሚኒስትሯ በአዲሱ ኃላፊነታቸው ዓለም አቀፍ አጋርነቶች እንዲጠናክር እና አገራት ወረርሽኞችን ለመከላከል ለሚያደርጉት ኢንቨስትመንት የሚሰጠውን ድጋፍ በበላይነት በመምራት ለዉጥ እንደሚያመጡ ፈንዱ ያለዉን እምነት ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር መቅደስ ኃላፊነቱን የተረከቡት ከሩዋንዳ ጤና ሚኒስትር ከሆኑት ከዶ/ር ሳቢን ንሳንዚማና ሲሆን፣ ሚኒስትሯ ባስተላለፉት መልዕክት የህብረተሰባችንን ህይወት መታደግ የሚችልና የዓለምን የጤና ደህንነት ዋስትናን የሚያረጋግጥ ጠንካራ የጤና ስርዓት በመገንባት ለትዉልድ ማስተላለፍ አለብን ብለዋል።
Minister of Health Dr. Mekdes Daba elected as Co-Chair of the Pandemic Fund Board
____________
Minister of Health Dr. Mekdes Daba has been elected as a Co-Chair of the Pandemic Fund Governing Board.
The Pandemic Fund is a multilateral financing mechanism established by the global community to help build capacity in low- and middle-income countries to prevent, detect, and respond rapidly to public health emergencies. The Fund expressed its confidence that, in her new role, the Minister will bring about change by overseeing the strengthening of international partnerships and the support provided for investments made by countries to prevent pandemics.
Dr. Mekdes took over the responsibility from Dr. Sabin Nsanzimana, the Minister of Health of Rwanda. In her message, the Minister stated that we must build and pass on to future generations a strong health system that can save the lives of our society and ensure global health security.