30/07/2026
የአዳሬ አጠቃላይ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት 4ኛ ሩብ ዓመት የህዝብ ፎረም መድረክ አካሄደ።
ሆስፒታሉ የ2018በጀት ዓመት የ4ኛ ሩብ ዓመት የህዝብ ውይይት መድረክ ያካሄደ ስሆን በፎረሙ ላይ ከሁሉም ክፍለ-ከተማ የተወጣጡ የህዝብ ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡
በመርሀግብሩ መሰረት ተሳታፊዎች ሆስፒታሉ እየሰጠ ያለውን አገልግሎት እና በቅርቡ ተመርቆ በከፊል አገልግሎት የጀመረውን የማስፋፊያ ግንባታ ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡ ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት በጥራት ገንብቶ ላጠናቀቀው የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምስጋና አቅርበዋል።
ከጉብኝቱ በኋላ የሆስፒታሉ ዓመታዊ አፈጻጸም ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል፤ በአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት፤ በመድሀኒት እና ግብዓት አቅርቦት እና አስተዳደራዊ ስራዎች ያሉበትን ደረጃ በተሳታፊዎች ተገምግሞ ጠንካራ አፈጻጸሞች ተጠናክረው እንቀጥሉ እና መሻሻል ያለባቸው ነጥቦች ላይ በትኩረት እንዲሰራ ሀሳብ አስተያየት ሰጥተዋል፡፡
ከዝህም ባሻገር ህንጻው በሙሉ አቅሙ አገልግሎት እንድሰጥ ቀሪ ጉዳዮች እና ዘመናዊ የህክምና መሳሪያዎች በመንግሰት በኩል እንዲሟሉ ሁሉም የበኩሉን ጥረት ማድረግ እንዳለበት አሳስበዋል።
ከተሳታፊዎች ለተነሱ አስተያየቶች እና ጥያቄዎች የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዘነበ ቱርጨ ምላሽ ሰጥተው ቀሪ ስራዎችን በጋራ በመረባረብ ለህብረተሰቡ የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆናቸው ገልጸው ተሳታፊዎችን አመስግነው መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።
ሐምሌ 22/2018 አዳሬ አ/ሆስፒታል ሀዋሳ።