Nigist Eleni Hospital-WCU

Nigist Eleni Hospital-WCU Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Nigist Eleni Hospital-WCU, Hospital, Hossana.
(1)

Nigist Eleni Mohammed Memorial Comprehensive Specialized Hospital is Wachemo University's Medicine and Health Science College Hospital with almost all the specialities

በሴቶችና ህጻናት ላይ ለሚደርሱ ጥቃቶች የህክምና ማስረጃ የሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸሰኔ 13/2018 ዓ/ም********//********በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ ...
20/06/2026

በሴቶችና ህጻናት ላይ ለሚደርሱ ጥቃቶች የህክምና ማስረጃ የሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገለጸ
ሰኔ 13/2018 ዓ/ም
********//********

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕረሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአንድ ማዕከል አገልግሎት አማካኝነት፤ ከሀድያ ዞን ከተለያዩ ወረዳዎች ከተወጣጡ የፍርድ ቤት ዳኞች፣ ዓቃቤ ህጎች፣ መርማሪ ፖሊሶች እና በሆስፒታሉ በአንድ ማዕከል አገልግሎት ውስጥ (One-Stop Center) ከሚሰሩ የሕክምና ባለሙያዎች ጋር በሆሳዕና ከተማ በተደረገ ውይይት በሴቶችና ህጻናት ላይ ለሚደርሱ ጥቃቶች የህክምና ማስረጃ የሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑ ተገልጿል።

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የጤና ትምህርትና ሕክምና አገልግሎት ኮርፖሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ተክሌ እጃጆ በንግግራቸው ወቅት እንደገለጹት፦ በአሁኑ ሰአት የሆስፒታሉ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተጠናከረ መልኩ እየሰራ እንደሚገኝ በመጠቆም፤ በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት በአንድ ማዕከል (One-Stop Center) ከሚሰጠው የሕክምና አገልግሎት በተጨማሪ፣ ለተጎጂዎች የስነ-ልቦና ድጋፍ ይሆን ዘንድ የ72 ሰዓት ማቆያ እንዲሁም የሕፃናት የስነ-ልቦና ሕክምና ማዕከል በመደራጀት ላይ እንደሚገኝ በመግለጽ ጥራት ያለው የሕክምና ማስረጃ ለፍትህ አካላት ለማቅረብ በልዩ ሁኔታ ትኩረት ተሰጥቶበት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

አክለውም አቶ ተክሌ እንደተናገሩት ይህን መሰል ውይይቶች በሕግ ባለሙያዎችና በሐኪሞች መካከል ግልጽ አሰራርን ስለሚፈጥር ለፍትህ አሰጣጥ ሂደቱ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው በመጠቆም ይህንን ውይይት ወደፊትም ከፍትህ አካላት ጋር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

የሀዲያ ዞን የሴቶችና ሕፃናት መምሪያ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ቴሬዛ አለሙ እንደተናገሩት፦ ሆስፒታሉ በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት ያለውን ከፍተኛ ቁርጠኝነትን ይህ የተዘጋጀው የሐኪሞችና የሕግ ባለሙያዎች ውይይት ያሳያል በማለት ይህም በአንድ ማዕከል በሚሰሩ ፎረንሲክ ሐኪሞች፣ የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስቶች እና በሕግ ባለሙያዎች መካከል ጠንካራ የተግባቦት አሰራር ስለሚፈጥር፣ ጥቃቱን ለመከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል።

ከሆስፒታሉ ከአንድ ማዕከል አገልግሎት (one stop center) የተወጣጡ የህክምና ባለሞያዎች በሕክምና ማስረጃ ዙሪያ ሳይንሳዊ በሆኑ የቃላት መግለጫዎች ላይ እንዲሁም ከመድረኩ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን በሴቶችና ሕፃናት ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመከላከል ልዩ ትኩረት አድርገው እንደሚሰሩም ተናግረዋል።

ሰኔ 13/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

19/06/2026
በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለ 4ኛ አመት የ አንስቴዝያ ተማሪዎች ሲሰጥ የቆየው Qualification ፈተና ተጠናቀቀሰኔ 11/2018 ዓ/ም********//*********...
18/06/2026

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ለ 4ኛ አመት የ አንስቴዝያ ተማሪዎች ሲሰጥ የቆየው Qualification ፈተና ተጠናቀቀ
ሰኔ 11/2018 ዓ/ም
********//*********

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ በህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በአንስቴዝያ ትምህርት ክፍል እየተማሩ ለሚገኙ የ 4ኛ አመት የአንስቴዝያ ተማሪዎች በንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለተከታታይ 4 ቀናት ሲሰጥ የቆየው Qualification ፈተና በሰላም ተጠናቋል።

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና አይንስታይን ኮሌጅ የአንስቴዝያ ት/ክፍል ሀላፊ የሆኑት አቶ ተከተል አበበ በንግግራቸው እንደገለጹት፦ ፈተናው ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በመጡ መምህራን ሲሰጥ መቆየቱን በመናገር የትምህርት ጥራቱን ከፍ ለማድረግ ይህን መሰል ፈተናዎች የሚኖራቸው አስተዋጽኦ ከፍ ያለ መሆኑን ገልጸዋል።

አክለውም አቶ ተከተል እንደተናገሩት ተፈታኞች በቀጣይ በሞያቸው ማህበረሰቡን በትጋትና በታማኝነት ማገልገል እንዳለባቸው አሳስበው ፈተናው በተሳካ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ ትብብር ላደረጉ ባለድርሻ አካላት ሁሉ ከፍ-ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ሰኔ 11/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

15/06/2026

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህጻናት የአይን ህክምና መስጫ ክፍል አሁናዊ ገጽታው !!(ሰኔ 5/2018 ዓ/ም)
12/06/2026

የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የህጻናት የአይን ህክምና መስጫ ክፍል አሁናዊ ገጽታው !!
(ሰኔ 5/2018 ዓ/ም)

የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎትን በማሻሻል የእናቶችና ህፃናትን ሞት መቀነስ እንደሚገባ ተገለጸ ።ሰኔ 2/2018 ዓ/ም******//********“Engender Health Ethiopian” የተሰኘ ...
09/06/2026

የቤተሰብ ዕቅድ አገልግሎትን በማሻሻል የእናቶችና ህፃናትን ሞት መቀነስ እንደሚገባ ተገለጸ ።
ሰኔ 2/2018 ዓ/ም
******//********

“Engender Health Ethiopian” የተሰኘ ግብረ-ሰናይ ድርጅት ከማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ጤና ቢሮ እና ከዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ጋር በጋራ በመተባበር ከተለያዩ የጤና ተቋማት ለተወጣጡ የጤና ባለሞያዎች ቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ዙሪያ ለተከታታይ አምስት ቀናት የሚቆይ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል።

በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የእናቶች፣ ህጻናት እና የስነ ምግብ ዳ/ዳይሬክተር ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ተስፋዬ ሌጂሶ በንግግራቸው ወቅት እንደገለጹት፦ ጤናማ እና የበለፀገ ህብረተሰብ ለማፍራት የቤተሰብ እቅድ አገልግሎቶችን ይበልጥ ማሻሻል እንደሚያስፈልግ ገልጸው ይህም የእናቶች እና ህጻናትን ሞት ለመቀነስ የሚኖረው አስተዋጽኦ ወሳኝ ነው ቀማለት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የእናቶች እና ህፃናት ሞትን ለመቀነስና በትኩረት መስራት እንደሚጠበቅባቸው አውስተዋል።

አያይዘውም በእናቶች እና ህፃናት ሞት ቅነሳ ላይ የሚፈለገውን ለውጥ ለማምጣት ሰልጣኞች ስልጠናውን በትኩረት ሊከታተሉት ይገባል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጤና ቢሮ የ Engender Health ሪጅናል ኮርድኔተር የሆኑት አቶ ሀያቱ መሃመድ በንግግራቸው እንዳሉት፦ እናቶች ከወለዱ በሗላ የሚሰጥ የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ማስፋት አስፈላጊ እንደሆነ በመጥቀስ ከአላስፈላጊ እርግዝና ጋር ተያይዞ የሚመጣ የጨቅላ ህጻናት ሞትን ለመቀነስም የቤተሰብ እቅድ አገልግሎቱ ወሳኝ ነው ብለዋል።

አክለውም አቶ አያቱ መሃመድ እንዳሉት በንግስት እሌኒ ሆስፒታል የሚወልዱ እናቶች በርካታ መሆናቸውን ተከትሎ ይህ አይነቱ ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና የሚኖረው ጠቀሜታ ትልቅ ነው ብለዋል።

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል የተከታታይ ሙያ ማጎልበቻና ስልጠና አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ዓለሙ ኤርሲዶ እንደተናገሩት ከወሊድ በሗላ እናቶች የቤተሰብ እቅድ አገልግሎት መጠቀማቸው ያልተፈለገ እርግዝናን ለመከላከል ጠቀሜታው ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

ሰኔ 2/2018 ዓ.ም
የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት !!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

08/06/2026

First batch Pediatrics and Child Health Speciality graduates of Wachemo University, 2026!!
25/05/2026

First batch Pediatrics and Child Health Speciality graduates of Wachemo University, 2026!!

ሆስፒታላችን Human Bridge ከተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ ግንቦት 8/2018 ዓ.ም********//********የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰ...
16/05/2026

ሆስፒታላችን Human Bridge ከተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ
ግንቦት 8/2018 ዓ.ም
********//********
የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በዛሬው እለት Human Bridge ከተሰኘ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በሆስፒታሉ የሚሰጡ የህክምና አገልግሎቶችን እና መማር ማስተማሩን ለመደገፍ የሚሆን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል።

በዕለቱም የመግባቢያ ሰነዱን የተፈራረሙት የዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አካ/ም/ቴክ/ሽ/ማ/አገ/ም/ፕሬዚዳንት የሆኑት ዶ/ር ሳራ ሽኩር እንደተናገሩት ፦ መማር ማስተማሩን ይበልጥ ለማዘመን እና ለማሻሻል ይህን መሰል የጋራ መግባቢያ ሰነድ የሚኖረው ጠቀሜታ ላቅ ያለ መሆኑን በማንሳት በቀጣይም ከ ድርጅቱ ጋር ሌሎች ስራዎችንም በጋራ እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ የንግስት እሌኒ መሃመድ መታሰቢያ ኮምፕርሔንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ይድነቃቸው ደዳቸው በንግግራቸው እንደገለጹት፦ ግብረሰናይ ድርጅቱ በየካቲት ወር 2018 ዓ.ም ወደ ሆስፒታሉ በመምጣት ጉብኝት ማድረጉን በማስታወስ ይህ የመግባቢያ ሰነድ መፈረሙ ለሆስፒታሉ ብሎም ለህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጁ የሚኖረው ተቀሜታ ከፍ ያለ ነው ብለዋል።

አክለውም ዳይሬክተሩ እንደተናገሩት፤ ማህበረሰብ ይበልጥ ሊጠቀም የሚችለው ጥራቱን የጠበቀ መማር ማስተማርና የህክምና አገልግሎት ሲኖር መሆኑን በመግለጽ ዛሬ የተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ በዚህ ረገድ የሚኖረው አስተዋጽኦ ከፍተኛ ነው ብለዋል።

የ Human Bridge Regional Director የሆኑት ዶ/ር አዳሙ አንለይ እንደተናገሩት ዛሬ የተፈረመው የመግባቢያ ሰነድ በሆስፒታሉ ውስጥ የሚሰጡ የህክምናና የመማር ማስተማር ስራዎችን ይበልጥ እንደሚያግዝ በመግለጽ ሁሌም ከፍ ያለ ውጤት የሚመጣው በጋራ መስራት ውስጥ እንደሆነም ተናግረዋል።
አክለውም ዶ/ር አዳሙ እንደገለጹት፤ ድርጅቱ የተለያዩ የህክምና መሳሪያዎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ከ ሲውድን ሀገር በማስመጣት ለሆስፒታሉ እንደሚያስረክቡም ተናግረዋል።

MFA Immunity Director የሆኑት አምባሳደር በላቸው አንሺሶ በንግግራቸው እንደገለጹት፦ Human Bridge ላለፉት አያሌ አመታት በርካታ የጤና ተቋማትን ለማዘመን ድጋፍ እያደረገ የሚገኝ ግብረሰናይ ድርጅት መሆኑን በማስታወስ እንደነዚህ ካሉ ስመ-ጥር ድርጅቶች ጋር በጋራ መስራት ለሆስፒታሉ የሚሰጠው ጠቀሜታ ትልቅ እንደሚሆን ተናግረዋል።

የካቲት ወር 2018 ዓ.ም ላይ Human Bridge በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/ስ/ሆስፒታል በመምጣት ጉብኝት ማድረጉ የሚታወስ ነው።

ግንቦት 8/2018 ዓ.ም
ዘገባው በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ ን/እ/መ/መ/ኮ/እ/ ሆስፒታል የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ነው!!!
Let Your light shine in the Society!!
ስለ ጤናዎ ለማማከር ዘውትር ከ ሰኞ-እሁድ በነጻ የስልክ መስመር 6712 ላይ ይደውሉ!!

Address

Hossana
42528

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nigist Eleni Hospital-WCU posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category