19/08/2026
ለወንዶ ገነት መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቦርድ ሰብሳቢ፣
ክቡር የሰሜናዊ ሲዳማ ዞን ኃላፊ አቶ ፃድቁ በጥሶ፣
ለወንዶ ገነት ከተማ አስተዳደር ኃላፊ ክቡር ኢንጂነር ተመስገን ተረፌ፣
እና ለወንዶ ገነት ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ ክቡር አቶ ሁሴን ከድር።
ጉዳዩ፦ በወንዶ ገነት መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እየተከሰቱ ስላሉ አስተዳደራዊ እና የፋይናንስ ክፍተቶች ምርመራ እንዲደረግ ስለመጠየቅ
ክቡራን ኃላፊዎች፣
በወንዶ ገነት መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል በአሁኑ ወቅት እየተከሰቱ ያሉ አንዳንድ አስተዳደራዊ፣ የሥራ አመራር እና የፋይናንስ ክፍተቶች በግልጽ ደረጃ እየታዩ ስለሆነ፣ ጉዳዩ በአግባቡ እንዲመረመርና ተገቢው እርምጃ እንዲወሰድ በትህትና እናሳውቃለን።
1. የሥራ አመራር እና የዱቲ ክፍያ ጉዳይ
አቶ ታደለ ተሰማ፣ የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ፣ የሆስፒታሉን ማኔጅመንት በመወሰን በአንድ ሰዓት 330 እና ከዚያ በላይ የዱቲ ሰዓት እንዲያገኙ ያለ ግልጽ መመሪያና ፈቃድ 31,862.88 ብር ወደ አካውንታቸው እንዲገባ መደረጉን የሚያሳይ ማስረጃ እንዳለ ተገንዝበናል። ስለሆነም ጉዳዩ በሰነድ እንዲጣራ እንጠይቃለን።
2. የአቶ ገዜሀኝ ወቃዮ የዱቲ ክፍያ
አቶ ገዜሀኝ ወቃዮ 120 ሰዓት እና ከዚያ በላይ የዱቲ ሰዓት ወደ ገንዘብ ሲቀየር 8,919.00 ብር መከፈሉን የሚያሳይ መረጃ እንዳለ ተገንዝበናል። ይህም ክፍያ በሚመለከተው መመሪያ መሠረት መፈጸሙን እንዲጣራ እንጠይቃለን።
3. የኦዲት እና የግምገማ ሥራን በተመለከተ
አቶ ቡዙነህ ቡርቃ በሆስፒታሉ ውስጥ ኦዲት በሚያካሂዱበት ወቅት የሚያገኟቸውን findings በተመለከተ ሪፖርት እንዳያቀርቡ ገንዘብ እንዲሰጣቸው ይጠይቃሉ የሚል መረጃ ደርሶናል። ይህ ክስ እውነት ከሆነ በኦዲት ሂደት ነፃነትና ገለልተኛነት ላይ ከፍተኛ ጥያቄ የሚያስነሳ በመሆኑ በአግባቡ እንዲመረመር እንጠይቃለን።
በተጨማሪም ሆስፒታሉ በ12 ወራት ውስጥ 18,000,000 ብር ማሰባሰብ የሚጠበቅበት ሆኖ፣ በ9 ወር ግምገማ ወቅት 9,000,000 ብር መሰብሰቡን የሚያሳይ ሪፖርት መኖሩን ተመልክተናል። ይህም በሰነድ እንዲጣራ እንጠይቃለን።
በተጨማሪም እነዚህን ክፍተቶች ለሚያሳዩ ግለሰቦች ተገቢው የሥራ ኃላፊነት እንዲሰጥ እና የዱቲ ሰዓት እና ክፍያ በመመሪያ መሠረት ብቻ እንዲወሰን እንጠይቃለን።
4. የአቶ ገታሁን ሳሙኤል ጉዳይ
አቶ ገታሁን ሳሙኤል ከበላም ይብላ በሚል አመለካከት ሳይሆን፣ በሥራቸው የሚታመኑ፣ ትጉህና በሥራ ላይ ብቃት የሚያሳዩ ሠራተኛ መሆናቸውን ለመግለጽ እንወዳለን።
5. የዱቲ ሰዓት አጠቃቀምና የ“ሳደን ሱፐርቪዥን” ጉዳይ
እነዚህ ሰዎች ከፍተኛ የዱቲ ሰዓት የሚያገኙበት ምክንያት ሲጠየቁ “ሳደን ሱፐርቪዥን እንገባለን” የሚል መልስ እንደሚሰጡ ይነገራል።
ነገር ግን በመንግሥት የሥራ ሰዓት ውስጥ በሥራ ቦታቸው በመገኘት የሚጠበቅባቸውን ሥራ ሳይሠሩ ተጨማሪ የዱቲ ሰዓት እንዲከፈላቸው መደረጉ ካለ ይህ በግልጽ ሁኔታ እንዲመረመር ያስፈልጋል።
6. የግዥ እና የአቅርቦት ሂደት
በሆስፒታሉ ውስጥ ብዙ የሥራ እቃዎች የሚገዙበት ሂደት በግልጽ ጨረታ እና በተገቢው የግዥ ሥርዓት መፈጸሙን ማረጋገጥ ያስፈልጋል።
በተለይ የሕትመት እቃዎችን በተመለከተ “ባባ” ተብላ የምትጠራ አቅራቢ ለ6 ዓመታት ያለ ግልጽ የጨረታ ሂደት የግብር ሕትመት እቃዎችን ብቻዋን እያቀረበች እንደሆነና በየወሩ ከ400,000 እስከ 500,000 ብር የሚደርስ ወጪ እንደሚደረግ መረጃ አለ።
ስለሆነም የግዥው ሂደት፣ የጨረታ ሰነዶች፣ የውል ስምምነቶች፣ የክፍያ ማስረጃዎች እና የአቅርቦት ሂደቱ በአግባቡ እንዲመረመር እንጠይቃለን።
7. የምርመራ እና የሠራተኞች ፎረም ጥያቄ
ስለ አቶ ታደለ ተሰማ እና ስለ ሆስፒታሉ አስተዳደር ተጨማሪ መረጃና ማስረጃ በእጃችን ያለ ሲሆን፣ ጉዳዩ በተገቢው አካል እንዲመረመር እንጠይቃለን።
በተጨማሪም ሠራተኞች በነፃነት ሀሳባቸውን የሚያቀርቡበት የStaff Forum በቅርቡ እንዲዘጋጅ፣ እነዚህ ጉዳዮችም በግልጽ እንዲወያዩባቸው እንጠይቃለን።
የመጨረሻ ጥያቄ
ከላይ የተጠቀሱት ጉዳዮች እውነተኛነታቸው በሰነድና በማስረጃ እንዲረጋገጥ፣ ከተረጋገጠም በሕግና በመመሪያ መሠረት ተገቢው እርምጃ እንዲወሰድ፣ የሆስፒታሉም አስተዳደር በግልጽነት፣ በተጠያቂነትና በፍትሐዊነት እንዲመራ በትህትና እንጠይቃለን።
“ለባን በአንድነት እንከላከል!”
Via Inbox