Doc Book

Doc Book � Writer only

18/08/2026

DREAM BUILDERS REAL ESTATE — የህልምዎ ቤት እዚህ ነው!
🏙️ DREAM BUILDERS REAL ESTATE 🏙️
✨ 5⭐ እና VIP የመኖሪያ አፓርትመንት ✨
📍 CMC — ከAfrican Convention Center ፊት ለፊት
ዘመናዊ አርክቴክቸር፣ የተሟላ አገልግሎት፣ ደህንነት እና የከፍተኛ ደረጃ ኑሮን በአንድ ላይ ያጣመረ ልዩ የመኖሪያ ፕሮጀክት!
🏢 7 ዘመናዊ ብሎኮች
👑 2 VIP ብሎኮች
🤖 AI የታገዘ ዘመናዊ የደህንነት ስርዓት
📐 23,000 ካሬ ሜትር ጠቅላላ የፕሮጀክት ስፋት
💰 ልዩ የክፍያ እድል!
🔥 10% ብቻ ቅድመ ክፍያ
በካሬ 98,888ብር ብቻ
🔥 በ10 ዙር ክፍያ — ያለ የዋጋ ጭማሬ
🔥 100% ሙሉ ክፍያ — 30% ቅናሽ
🔥 ከቅናሹ በኋላ በካሬ 73,000 ብር ብቻ!
🏠 የቤት አማራጮች
🛏️ 1 መኝታ: 73.6 ካሬ | 76 ካሬ
🛏️🛏️ 2 መኝታ: 106 | 112 | 117 | 127 ካሬ
🛏️🛏️🛏️ 3 መኝታ: 141 | 152 | 158 | 184 | 192 ካሬ
👑 6 መኝታ: 304 | 312 | 315 ካሬ
➕ የሰራተኛ ክፍል ያላቸው ተጨማሪ አማራጮችም አሉ።
🌟 PREMIUM AMENITIES
🏊 2 የመዋኛ ገንዳዎች
🏋️ ዘመናዊ ጂም & ሳውና
🏀 የባስኬትቦል ሜዳ
🧒 የልጆች መጫወቻ — ውስጥ & ውጭ
🚗 የተመደበ ፓርኪንግ + EV Charging
🌳 ሰፊ አረንጓዴ ቦታ
🛍️ ዘመናዊ የገበያ ቦታ
🏃 የሩጫ መንገድ
🚴 የብስክሌት መንገድ
🏨 5⭐ Reception & Service
✨ የተሻለ ኑሮ፣ የተሻለ አካባቢ፣ የተሻለ ኢንቨስትመንት! ✨
📲 ለበለጠ መረጃ እና ቤትዎን ለመያዝ በWhatsApp ያግኙን፦
📞 0913 840 464
📞 0911 835 907
🏡 DREAM BUILDERS REAL ESTATE
❤️ ሕልምዎን እንገነባለን!

በጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል አራት ህፃናትን በሰላም የተገላገለችው እናት በሆስፒታሉ በተደረገላት ክትትል  በሙሉ ጤንነት ልጆችዋን ታቅፋ ወደ ቤትዋ ተሸኘች              አአ ጤ...
18/08/2026

በጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል አራት ህፃናትን በሰላም የተገላገለችው እናት በሆስፒታሉ በተደረገላት ክትትል በሙሉ ጤንነት ልጆችዋን ታቅፋ ወደ ቤትዋ ተሸኘች

አአ ጤና ቢሮ ነሀሴ 12/2018

​በለፈው ሳምንት አራት ህፃናትን በሆስፒታሉ በሰላም የተገላገለችው የ26 አመት ወጣት እናት ፣ላለፉት ስምንት ቀናት በተደረገላቸው ክትትል በጥሩ ጤንነት ላይ በመሆናቸው ቆይታቸውን አጠናቀው ወደ ቤት ተሸኝተዋል።

​ህፃናቱ በተወለዱበት ወቅት የነበራቸው ክብደት ከ1 ነጥብ 4 እስከ 1 ነጥብ 9 ኪሎ ግራም የነበረ በመሆኑ፣ በጨቅላ ህፃናት ማጠናከሪያ ክፍል በማሞቂያ ውስጥ ገብተው አስፈላጊው ከፍተኛ የህክምና እና የነርሲንግ ክትትል ሲደረግላቸው ቆይተዋል።

​በተደረገላቸው የቅርብ ክትትል እና እንክብካቤ አራቱም ህፃናት እንዲሁም እናታቸው በጥሩ የጤና ሁኔታ ላይ የሚገኙ በመሆናቸው ወደ ቤታቸው እንዲሸኙ ተደርጓል።

01/08/2026
28/07/2026

የሕፃናት ቁርጠት ምንድነው?

የሕፃናት ቁርጠት (infantile colic) በተወለዱ በመጀመሪው ወር በጨቅላ ህጻናት ላይ የሚከሰት ሲሆን ይህንንም ክስተት ለማወቅ የምንጠቀምበት መስፈርት የሶስትዮሽ ህግ (Rule of 3s) ይባላል።

ይሄውም በቀን ለሶስት ሰአትና ከዛ በላይ ፣ በሳምንት ለሶስት ቀናትና ከዛ በላይ እንዲሁም ለሶስት ሳምንታትና ከዛ በላይ የሚቆይ የለቅሶና መነጫነጭ ስሜት ነው። አብዛኞቹ የቁርጠት ህመሞች በተደጋጋሚ ጊዜ ሰአት ለይተው የሚከሰቱ ሲሆን ቁርጠቱ ማታ ማታ የተለመደ ነው ።

በየትኛው ዕድሜ ይከሰታል?

አንድ ህፃን ከተወለደ በኋላ ሁለት እስከ ሶስት ሳምንት ውስጥ ይጀምራል። ይህ ሁኔታ በስድስት ሳምንት እድሜ እጅግ ይጨምራል። ነገር ግን የልጁ እድሜ እየጨመረ ሲሄድ ማለትም በ3–4 ወር ላይ በራሱ ያለምንም ህክምና ይቆማል። እድሜቸው አራት ወር እና ከዚያ በላይ የሆኑ ህፃናት ላይ የተለመደ ክስተት አይደለም ስለዚህ ከአራት ወር እድሜ በኋላ ከልክ ያለፈ ለቅሶ የሌሎች ጤና ችግሮች ምልክት ሊሆን ስለሚችል ወላጆች ትኩረት ሰጥተው ልጆቻቸውን ወደ ጤና ተቋማት በመውሰድ ማሳየት ይኖርባቸዋል። አልፎ አልፎ ግን በጣም ጥቂት ህጻናት ላይ እስከ ዘጠኝ ወር ሊዘልቅ ይችላል።

መንስኤዎች

በመንስኤው ላይ በህክምና ባለሙያዎች ዘንድ ወጥ የሆነ መግባባት ባይኖርም የአንጀትና ባጠቃላይ የስርአተ ልመት ኢንዛይሞች ከአለመጎልመስ ጋር የተያያዘ ነው ተብሎ ይታሰባል።

መፍትሄው

የቁርጠት መንስኤ የተለያዩ ምክኒያቶች በመሆናቸው እንዲሁም የህመሙ ባህሪ ከልጅ ልጅ ስለሚለያይ ለቁርጠት ወጥ የሆነ ህክምና የለውም። የተለያዩ ጥናቶች እንደሚያሳዩት መድሀኒት መስጠት ለቁርጠት ብዙ ጠቀሜታ አይሰጥም።

ነገር ግን በወላጆች በኩል ቁርጠቱን ለማስታገስ ሊደረጉ ሚገባቸው ነገሮች የሚከተሉት ናቸው ።

*ህጻኑን ዘና እንዲልና እንዲረጋጋ የሚያደርጉ ለምሳሌ ገላን በሙቅ ውሀ ማጠብ ለስለስ ባለ ብርድ ልብስ መጠቅለልና ጥንቃቄ በተሞላበት መልኩ ህጻኑን መወዝወዝ( rocking motion)፣ ለስላሳ ሙዚቃ መክፈትና እሹሹ እያሉ ማረጋጋት ህጻኑ ህመሙ ቀለል እንዲልለት ይረዳል።
*ካጠቡ በኋላ ማስገሳትና ከልክ በላይ ማጥባትን ማስወገድ።

ለረጅም ሰአት ህጻኑ በማልቀሱ የሚያስከትለው ችግር

ህፃኑ ለረጅም ሰአት በማልቀሱ የሚመጣ ጉዳት የለም። ህጻኑ የአካል ጥንካሬው ጥሩ ከሆነ፣ በደምብ የሚጠባ እንዲሁም በጥሩ የእድገት ደረጃ ላይ ካለና የ ትኩሳት ምልክት ካልታየበት ከሰላሳ ደቂቃ በላይ ቢያለቅስም ያን ያህል አሳሳቢ አይደለም። ስለዚህ ወላጆች ህፃናትን ለማረጋጋት ከሚጠቀሙበት መንገዶች ውጪ ከ አምስት እስከ አስር ደቂቃ ህፃኑ እንዲያለቅሱ በመተው ራሱን በራሱ እንዲያረጋጋ ማድረግ ይቻላል።

ምርመራ

ለቁርጠት የሚደረግ ምርመራ የለም። አብዛኛውን ጊዜ ቀደም ሲል በተጠቀሰው መስፈርት (Rule of 3s) ማወቅ ይቻላል ነገር ግን ቁርጠቱ ሲከሰት ህፃኑ በህፃናት ህክምና ባለሙያ እንዲታይ በማድረግ የችግሩ መንስኤ ቁርጠት ወይም ሌላ ህመም መሆኑን ማወቅ ይቻላል። ህጻኑ በህጻናት ህክምና ስፔሻሊስት ከታየ በኋላ ከአንጀት ጋር የሚያያዝ ችግርን ከተጠረጠረ ራጅ ወይም አልትራሳውንድ ምርመራ እንደሁኔታው ሊታዘዝ ይችላል።

ቁርጠት ላይሆን ሚችልባቸው ሁኔታዎች

* ለቅሶው ከተለመደው በጣም ከረዘመና ከህፃኑ ባህሪ ጋር ባልተለመደ መልኩ የሚከሰት ከሆነ ።
* የንቃት መቀነስ ካለ
* ትኩሳት
* ጡት አለመጥባት ወይም ፍላጎት መቀነስ
*የሆድ መነፋት
* ተደጋጋሚ ትውከት
* ያልተለመደ የሆድ ድርቀት ወይም ተቅማጥ
* እና በፊንጢጣ የሚወጣ ደም
ከላይ የተጠቀሱት ምልክቶች ካሉ ቶሎ ወድ ጤና ተቋማት በመሄድ ማሳየት ያስፈልጋል።

ጤናማ ህፃናት ብሩህ ነገ!
ዶ/ር መላኩ ሞገስ: የህፃናት ህክምና ስፔሻሊስት: ወልድያ ዩንቨርስቲ

ለስፐርም ጥራት ማሽቆልቆል ምክንያት የሆኑ 9 ዋና ዋና ነገሮች! የአንድ ወንድ የመውለድ ብቃት  በቀጥታ ከሚያደርጋቸው የዕለት ተዕለት ልምዶች እና ለአንዳንድ ነገሮች ከሚጋለጥባቸው ሁኔታዎች ...
27/07/2026

ለስፐርም ጥራት ማሽቆልቆል ምክንያት የሆኑ 9 ዋና ዋና ነገሮች!

የአንድ ወንድ የመውለድ ብቃት በቀጥታ ከሚያደርጋቸው የዕለት ተዕለት ልምዶች እና ለአንዳንድ ነገሮች ከሚጋለጥባቸው ሁኔታዎች ጋር የተያያዘ ነው።

1. በወንድ የዘር ፍሬ ላይ የሚደርስ ከፍተኛ አደጋ ወይም ጉዳት የሰውነታችንን የበሽታ መከላከያ ሥርዓት በማነቃቃt ለወንዶች መካንነት ምክንያት ሊሆን ይችላል። በአንፃሩ፣ ቀለል ያሉ የወንድ ዘር ከረጢት መላላጦችና መጋጨቶች የተለመዱ ቢሆኑም አብዛኛውን ጊዜ በመውለድ ብቃት ላይ የሚያመጡት ተፅዕኖ የለም።

2. ሲጋራ ማጨስ; የትምባሆ ጭስ የዘር ፈሳሽ ትኩረትን ፣ ወደፊት የመንቀሳቀስ ብቃትን ፣ ውጫዊ ቅርጽን እና የህይወት ቆይታን ይቀንሳል። በተጨማሪም ስፐርም ወደ እንቁላል የመግባት ብቃቱን እንዲያጣ ያደርጋል።

3. ስቴሮይድስ: ለተለያዩ ዓላማዎች (ለምሳሌ ለሰውነት ማሳደጊያ) የሚወሰዱ ውጫዊ ሆርሞኖች በአንጎላችን ውስጥ የሚገኘውን ፒቱታሪ ግላንድ ሆርሞን እንዳያመርት ያግዱታል። ይህ ደግሞ በጠቅላላው የዘር ፍሬ ምርትን ሙሉ በሙሉ ያቆማል።

4. አንዳንድ መድኃኒቶች: በርካታ የታዘዙ መድኃኒቶች በወንድ ዘር ሴሎች ላይ መርዛማ ተፅዕኖ በማሳደር ወይም የመራቢያ ሥርዓት መዋቅርን በማስተጓጎል መካንነትን ሊያስከትሉ ይችላሉ። ለአብነት ያህል፦ ኬቶኮናዞል ፣ ስፒሮኖላክቶን (spironolactone)፣ የደም ግፊት መድኃኒቶች ፣ ኤሪትሮማይሲን ፣ ኒትሮፉራንቶይን ፣ ጄንታማይሲን እና ቴትራሳይክሊን ይጠቀሳሉ።

5. ጥብቅ ልብሶች: ጥብቅ የሆኑ ሱሪዎችንና የውስጥ ሱሪዎችን መልበስ በታችኛው የሰውነት ክፍላችን ላይ ያለውን ሙቀት ይጨምራል። የወንድ የዘር ፍሬ ሙቀት በ 1°C ብቻ እንኳ ቢጨምር የስፐርም ክምችትን በ 40% ይቀንሳል። ለዚህ ነው በኢንፌክሽን (በከፍተኛ ትኩሳት) ወቅት የስፐርም ምርመራ ሲደረግ ምንም ዓይነት ስፐርም የማይገኘው።

6. ውፍረት: ከመጠን በላይ ክብደት ያላቸው ወንዶች፣ መደበኛ ክብደት ካላቸው ወንዶች ጋር ሲነፃፀሩ በመውለድ ችግር የመጠቃት ዕድላቸው በ 50% የላቀ ነው። ይህ የሚሆነው በስብ ሴሎች ውስጥ አንድሮጅን ሆርሞን ወደ ኢስትሮጅን ስለሚቀየርና ይህ ሂደት የወንድ ዘር ዕድገትን በአሉታዊ መልኩ ስለሚጎዳው ነው።

7. ፕታሌትስ: እነዚህ በፕላስቲኮች እና በመዋቢያዎች ውስጥ የሚገኙ ኬሚካሎች ናቸው። በሽንታቸው ውስጥ ከፍተኛ የፕታሌትስ መጠን የሚገኝባቸው ወንዶች የቴስቶስትሮን ሆርሞን መጠናቸው ዝቅተኛ ሆኖ ይገኛል። ዝቅተኛ ቴስቶስትሮን ማለት ደግሞ የመውለድ ችግር ማለት ነው።

8. አልኮል: ከመጠን በላይ መጠጣት የመውለድ ብቃትን በሚከተሉት መንገዶች ይጎዳል፦

👉🏿የቴስቶስትሮን ሆርሞንን በመቀነስ
👉🏿የፒቱታሪ ግላንድ ሆርሞኖችን በማሳነስ
👉🏿 የወንድ ዘር (ስፐርም) ምርትን እና ተግባርን በማስተጓጎል!

9. BPA (ቢፒኤ); ቢስፌኖል ኤ (Bisphenol A) በፕላስቲክ ዕቃዎች ውስጥ የሚገኝ ኬሚካል ሲሆን፣ የቴስቶስትሮን ሆርሞን መጠን እንዲቀንስ ያደርጋል።

እንወያይ፦
ከእነዚህ 9 ነጥቦች ውስጥ እናንተን ይበልጥ ያስገረማችሁ ወይም ቀደም ሲል የማታውቁት የትኛውን ነው? በተለይ ጥብቅ ልብስ መልበስና ውፍረት በዚህ ደረጃ ተፅዕኖ አላቸው ብላችሁ አስባችሁ ታውቃላችሁ?

አስተያየታችሁን በኮሜንት አጋሩን! 👇
ወንድ ወንድሞቻችንና ጓደኞቻችን ራሳቸውን እንዲጠብቁ Share በማድረግ መረጃውን አብዙላቸው!

በወንድ አካል ላይ ያለው የፕሮስቴት እብጠት (BPH) በወሲብ ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ የፕሮስቴት ሕክምናዎች የወንድ ብልት አለመቆም ችግርን (Erectile Dysfunction) ሊያስከትሉ ይ...
27/07/2026

በወንድ አካል ላይ ያለው የፕሮስቴት እብጠት (BPH) በወሲብ ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ

የፕሮስቴት ሕክምናዎች የወንድ ብልት አለመቆም ችግርን (Erectile Dysfunction) ሊያስከትሉ ይችላሉ?

የፕሮስቴት እብጠት (Benign Prostatic Hyperplasia - BPH) ካንሰር ያልሆነ የፕሮስቴት እብጠት ሲሆን ከ50% በላይ በሚሆኑ እድሜያቸው ከ50 በላይ በሆኑ ወንዶች ላይ የሚከሰት ነው።

የፕሮስቴት እብጠት ብቻውን አስጊ ባይሆንም ህክምናዎቹ በወሲብ ጤና ላይ ግን ተጽዕኖ ሊያሳድሩ ይችላሉ።

አንዳንድ መድሃኒቶች፣ በተለይ 5-አልፋ ሪዳክታዝ እንደፊናስቴሪድ (Finasteride) ያሉ ምርቶች የወሲብ ፍላጎትን መቀነስ እና በግብረ ስጋ ግንኙነት ወቅት የወንድ ብልት አለመቆም ችግርን ሊያመጡ ይችላሉ።

እንዲሁም አንዳንድ ቀዶ ህክምናዎች፣ ለምሳሌ የሚታወቀው Transurethral Resection of the Prostate (TURP) በወንድ ዘር መርጨት ሥርዓት ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል።

ይህም የወንድ ዘር ወደ ብልት ከመሄድ ይልቅ ወደ ሽንት ማጠራቀሚያ እንዲሄድ ያደርገዋል(Retrograde Ejaculation)።

አዳዲስ መመሪያዎች እነዚህን የጐንዮሽ ጉዳቶች ከሕክምናው በፊት ከታካሚው ጋር መወያየት እና የተሟላ ውሳኔ ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን ያስረዳሉ።

****
በ ዶ/ር እሌኒ ሞላ

መረጃ ምንጭ፣ European Association of Urology (EAU).

የደቡብ ወሎ ገዳም ጥቃትን በተመለከተ ፓትርያርኩ መግለጫ አወጡ፤ ተጠያቂዎች ለፍትሕ እንዲቀርቡ ጠየቁ።ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳ...
25/07/2026

የደቡብ ወሎ ገዳም ጥቃትን በተመለከተ ፓትርያርኩ መግለጫ አወጡ፤ ተጠያቂዎች ለፍትሕ እንዲቀርቡ ጠየቁ።

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት፣ በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በቦረና ወረዳ በግዮን አባይ ገዳመ አስቄጥስ ቅድስት አርሴማ፣ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶችና የእናቶች አንድነት ገዳም ላይ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. በተፈጸመው ጥቃት ላይ መግለጫ አውጥተዋል።

በመግለጫቸው፣ በጥቃቱ የመናንያን መነኮሳይያት ሕይወት በግፍ መጥፋቱን፣ በርካቶች መቁሰላቸውን እና በገዳሙና በንዋየ ቅድሳቱ ላይ ውድመት መድረሱን ከሀገረ ስብከቱ መግለጫ በከፍተኛ ሐዘን መስማታቸውን ገልጸዋል።

በተመሳሳይም፣ በዚሁ ዕለት በሀድያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የአምልኮ ሥፍራ በኃይል መፍረሱና በምእመናን ላይ ጥቃት መድረሱ በመግለጽ ድርጊቱ የሚያሳዝንና በፍጹም ተቀባይነት የሌለው የተወገዘ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል።

ፓትርያርኩ እንዳሉት፣ የጸሎት፣ የትምህርት፣ የሰላምና የመንፈሳዊ እሴት ማዕከል የሆኑትን ገዳማት መጠበቅ የአንድ ሃይማኖት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ የሰው ልጅ ክብርን፣ የሕግ የበላይነትንና የሀገር ሰላምን የማስጠበቅ ኃላፊነት ያላቸው በየደረጃው የሚገኙ ባለሥልጣናትና የሕግ አስከባሪ አካላትም የሚመለከታቸው ጉዳይ መሆኑን አስገንዝበዋል።

አሰቃቂውን ጥቃት የፈጸሙ ተጠያቂዎች ለፍትሕ እንዲቀርቡ፣ ሌሎች ገዳማትና አድባራት ደኅንነታቸው እንዲጠበቅ እና ለተጎዱትም ተገቢው ድጋፍ እንዲደረግላቸው ጥሪ አቅርበዋል።

በመጨረሻም፣ ሕዝበ ክርስቲያንና መላው ኢትዮጵያውያን የጥቃቱ ሰለባ ከሆኑት ወገኖች ጋር በመንፈሳዊም ሆነ በስብአዊ ድጋፍ እንዲቆሙ አሳስበው፣ ለተበደሉት ፍትሕ፣ ለቆሰሉት ፈውስ፣ በግፍ ሕይወታቸውን ለተነጠቁት ዕረፍተ ነፍስ፣ ለቤተ ክርስቲያኒቱና ለሀገሪቱ ፍጹም ሰላም እንዲሰጥ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

የእነ አቶ ክርስቲያን ታደለ መዝገብ፡ የብይን መነበብ እንደገና ወደ 2019 ዓ.ም ተሸጋገረበሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት አቶ ክርስቲያን...
24/07/2026

የእነ አቶ ክርስቲያን ታደለ መዝገብ፡ የብይን መነበብ እንደገና ወደ 2019 ዓ.ም ተሸጋገረ

በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት አቶ ክርስቲያን ታደለ፣ አቶ ዮሐንስ ቧያለው እና ሌሎች ተከሳሾች መዝገብ ላይ ዛሬ ይሰጣል ተብሎ የተጠበቀው ዋና ብይን በድጋሚ ሳይሰጥ መቅረቱ ተገለጸ።

በዛሬው ዕለት በተካሄደው የችሎት ውሎ፣ ቀደም ሲል ፍርድ ቤቱ ከኢትዮ ቴሌኮም ጠይቆት የነበረው መረጃ በንባብ ተሰምቷል። የዶክተር ካሳ ተሻገር እና የጋዜጠኛ ቴዎድሮስን ስልክ ቁጥሮች በተመለከተ ተቋሙ በሰጠው ምላሽ፡

የስልክ ቁጥሮቹ ለረጅም ጊዜ ከአገልግሎት ውጭ ሆነው በመቆየታቸው ምክንያት ከአገልግሎት ውጭ የሆኑበት ጊዜ አብቅቷል።

በቴሌኮሙ ደንብና አሰራር መሰረትም ቁጥሮቹ ተነስተው ለሌሎች አዲስ ተጠቃሚዎች መተላለፋቸውን አረጋግጧል።

ተከሳሾቹ በችሎቱ ላይ በሰጡት አስተያየት፣ ያለ ምንም ውሳኔ ላለፉት ሦስት ዓመታት በእስር ላይ መቆየታቸው ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል።

"በተለያዩ ጥቃቅን ምክንያቶች ፍትህ እየተጓተተብን ነው። ችሎቱ ብይኑን ቀድሞ የሚያውቀው ከሆነ፣ በተራዘመ ቀጠሮ ፍትህ ከመዘግየት ይልቅ በአጭር ቀን ቀጥሮ ብይኑን ለምን አያነበውም?" ሲሉ ተከሳሾቹ አቤቱታቸውን አቅርበዋል።

የችሎቱ ዳኞች ለቀረበው ቅሬታ በሰጡት ምላሽ፡
ፍርድ ቤቱ ብይኑን ቀድሞ ያዘጋጀው ቢሆንም፣ በህግ አሰራር መሰረት ተከሳሽ ማረሚያ ቤት እያለ ባልተገኘበት ሁኔታ ውሳኔ ማንበብ አይቻልም።

ውሳኔ የማይነበበው ተከሳሹ ፍርድ ቤት አልመጣም ብሎ በእምቢተኝነት የቀረ እንደሆነ ብቻ መሆኑን የጠቀሰው ችሎቱ፤ አንደኛ ተከሳሽ የተከበሩ አቶ ዮሐንስ ቧያለው በህመም ምክንያት በመቅረታቸው ብይኑን ማነብ እንደማይቻል ገልጻል።

በዚህም መሰረት ታማሚው ተከሳሽ ተሻሏቸው በችሎት ሲገኙ ብይኑ የሚነበብ መሆኑ ተገልጾ፣ «ተከሳሾቹ መከላከያ ማስረጃ ያቅርቡ ወይስ በነፃ ይሰናበቱ?» በሚለው ነጥብ ላይ ብይን ለመስጠት ለጥቅምት 06 ቀን 2019 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከነሐሴ 01 እስከ መስከረም 30 ባሉት ሁለት ወራት የፍርድ ቤቶች የዕረፍት ጊዜ በመሆኑ ፍርድ ቤቶች በከፊል ዝግ ሆነው እንደሚቆዩ ይታወቃል።

ዘገባው የሸገር ኤፍ ኤም ነው

ጉርሻ page

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Doc Book posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share

Category