19/05/2026
ለዚህም ክብር በመብቃትዎ መላው የሥራ ባልደረቦችዎ የተሰማንን ኩራት እየገለጽን፣ ለቀጣይ የሥራ ዘመንዎ ስኬትንና ጤናን እንመኛለን!
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ባከናወነው 41ኛው የሕክምና ተማሪዎች ምርቃት ስነ-ስርዓት ላይ፣ ለታዋቂው የቀዶ ሕክምና ስፔሻሊስት ዶ/ር ዘኪ አብዱራህማን የሙካሽ ካባ እና የጋሻ ሽልማት በማበርከት ታላቅ እውቅና ሰጥቷቸዋል።
ዶ/ር ዘኪ የጉበት፣ የቆሽትና የሀሞት ቀዶ ሕክምና (Hepatobiliary Surgery) ሰብ-ስፔሻሊስት ሲሆኑ፣ በሙያዊ ብቃታቸው ብቻ ሳይሆን ለታካሚዎቻቸው ባላቸው ጥልቅ ተቆርቋሪነት፣ ለተማሪዎቻቸውም ባላቸው አርአያነት በጎንደር ሕዝብና በዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ዘንድ ልዩ ቦታ አላቸው።
በጎንደር ተምረው ለታላቅ ስመ-ጥርነት የበቁት ዶ/ር ዘኪ፣ ዩኒቨርሲቲው "የእኔ እኮ ነው" ከሚላቸው ድንቅ የሕክምና ዕንቁዎች አንዱ ናቸው። ለዚህም ክብር በመብቃትዎ መላው የሥራ ባልደረቦችዎ የተሰማንን ኩራት እየገለጽን፣ ለቀጣይ የሥራ ዘመንዎ ስኬትንና ጤናን እንመኛለን!
እንኳን ደስ አሎት! 💐🎊
አዲስ ህይወት አጠቃላይ ሆስፒታል
Addis Hiwot General Hospital
Source Hakim