26/08/2026
ወደርየለሽ ደስታ!
ሌሊት ነበር......
እኔም የወሊድ ምልክቶች መጀመራቸውን ስረዳ፣ በደስታና በፍርሃት መካከል ተወሰንኩ።
“ልጄ ዛሬ ሊመጣ ነው!” የሚለው ሀሳብ ደስ ያሰኘኝ ነበር፤ ነገር ግን “ወሊዱ እንዴት ይሆን?” የሚለው ጥያቄ ልቤን ያሸብረዉ ነበር።
ወደ ጋንዲ ሆስፒታል ስደርስ ነርሷ በፈገግታ ተቀበለችኝ። “አትፍሪ፣ ከአንቺ ጋር ነን” አለችኝ። ያ አንድ አረፍተ ነገር በውስጤ ያለውን ጭንቀት ትንሽ አረጋጋው።
ምጡ እየጠነከረ ሲመጣ ህመሙ ከባድ ነበር። እኔ ግን አንድ ነገር ብቻ ነበር የማስበው፤ “ልጄን ማየት እፈልጋለሁ!”
ሐኪሙ፣ ነርሶቹና የወሊድ ቡድኑ በየደቂቃው ከእኔ ጋር ነበሩ። እያበረታቱኝ፣ እያረጋጉኝ እና የሚያስፈልገኝን እርዳታ እየሰጡኝ ነበር።
ከትንሽ ጊዜ በኋላ የህፃኑ ድምፅ ተሰማ.....
ያ ድምፅ...
እስከዛሬ ድረስ ከህይወቴ የማልረሳው ድምፅ ነው።
እንባዬ በደስታ ፈሰሰ። ህመሙ፣ ፍርሃቱና ጭንቀቱ ሁሉ በአንድ ቅፅበት የጠፉ መሰለኝ። ልጄን ወደ እጄ ሲያስጠጉልኝ የመጀመሪያ ጊዜ አየሁት።
“እናት ሆኛለሁ!”
ያንን ቃል በውስጤ ስደግመው እንባዬን ማቆም አልቻልኩም።
የወሊድ ገጠመኜ ህመም ብቻ አልነበረም፤ ትዕግስት፣ ተስፋ፣ ፍርሃት፣ ፍቅርና በመጨረሻም የእናትነት ደስታ የተቀላቀለበት የህይወቴ ትልቁ ቀን ነበር።
ዛሬ ልጄን በእጄ ይዤ ሳየው አንድ ነገር እረዳለሁ፤ አንዳንድ ህመሞች ከባድ ቢሆኑም ከኋላቸው የሚመጣው ደስታ ከሁሉም በላይ ነው።
ጋንዲ አይኔን በአይኔ ያዩሁበት ልዩ ስፍራ ነዉ!
(ታሪኩ የወ/ሮ አይንዓለም እሸቴ ነዉ ።ግዜዉም ጥቅምት 12,1989 መሆኑን ልብ ይሏል!)