Amanuel mental specialized hospital

Amanuel mental specialized hospital Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Amanuel mental specialized hospital, Addis Ababa ethiopia Addis ketema subcity at the vicinity of Mesalemeya, Addis Ababa.

Emmanuel mental specialized hospital is apionner one which provides mental health care and treatment for about people who are from all corners of the nation and mental health rehabilitation services since it has been established in 1938

በዘርፉ ህመምን ከመቆጣጠር ባሻገር ስቃይን ማስታገስና የኑሮ ጥራትን ማሻሻል እንደሚገባ ተገለፀበ“Basic Pain and Palliative Care” አገልግሎት ላይ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተ...
05/09/2026

በዘርፉ ህመምን ከመቆጣጠር ባሻገር ስቃይን ማስታገስና የኑሮ ጥራትን ማሻሻል እንደሚገባ ተገለፀ
በ“Basic Pain and Palliative Care” አገልግሎት ላይ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ተሰጠ
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 30/ 2018 ዓ.ም – በህክምና ሂደት ወቅት ታካሚዎች የሚያጋጥማቸውን ህመምና ስቃይ በተገቢው ለመለየት፣ ለመገምገም፣ ለመቆጣጠርና ለማስታገስ የሚያስችል “Basic Pain and Palliative Care” አገልግሎት ላይ ያተኮረ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ከሆስፒታሉ ለተውጣጡ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች ተያያዥ የዘርፍ ባለሙያዎች በአዳማ ከተማ ተሰጠ።
ስልጠናው በአማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፋሚሊ ሜዲስን ስፔሻሊስት ሀኪም በሆኑት ዶ/ር ሚኪያስ ታደለና የህክምና አገልግሎት ጥራት ዳይሬክቶሬት ጋር በመተባበር ነው።
ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የስነ-አእምሮ ዲፓርትመንት ዳይሬክተር ዶ/ር ሉሉ በቃና ሲሆኑ በንግግራቸው “ የምንሰጠው አገልግሎት ማከምና ማዳን ብቻ ሳይሆን ጥንቃቄ የተሞላበት ህመምንና ስቃይን መቀነስ መቻል የጤና አገልግሎት ጥራት ወሳኝ አካል ነው” ብለዋል።
ዶ/ር ሉሉ እንደገለፁት የስልጠናው ዋና ዓላማ የታካሚዎችን ህመምና ስቃይ በአግባቡ በመረዳት ተገቢውን እንክብካቤና የህክምና ድጋፍ እንዲያገኙ የጤና ባለሙያዎችን እውቀትና ክህሎት ማጎልበት ነው ብለዋል።
ዶ/ር ሚኪያስ ታደለ በበኩላቸው ስልጠናው የጤና ባለሙያዎች የታካሚዎችን የህመም ደረጃ በተገቢው እንዲመዝኑ፣ ተገቢውን የህመም መቆጣጠሪያ አማራጭ እንዲመርጡና በህክምና ሂደቱ ውስጥ ሰው-ተኮር እንክብካቤን እንዲያጠናክሩ የሚያስችል ዕውቀትና ክህሎት ለማስጨበጥ ያለመ መሆኑን አብራርተዋል።
በተለይም የአእምሮ ህመም ያለባቸው ታካሚዎች ህመምና ስቃያቸውን የሚገልጹበት መንገድ ከሌሎች ታካሚዎች ሊለይ ስለሚችል ህመማቸውን በትክክል መለየትና መገምገም ልዩ ትኩረት የሚሻ መሆኑንም በማከል ገልጸዋል።
ፓሊያቲቭ ኬር (Palliative Care) ማለት ህመምን ማከም ብቻ ሳይሆን በከባድና ረጅም ጊዜ ህመም የሚሰቃዩ ታካሚዎችን በሙሉ የሰውነት እና የሰውነት ውጭ ፍላጎቶች በመመልከት የኑሮ ጥራታቸውን ለማሻሻል የሚሰጥ የተቀናጀ እንክብካቤ ነው።
አገልግሎቱ ከህመምና ከሌሎች አስጨናቂ ምልክቶች እፎይታ ከመስጠት ባሻገር የታካሚውን አካላዊ፣ ስነ-ልቦናዊ፣ ማህበራዊና መንፈሳዊ ፍላጎቶች በተቀናጀ መልኩ በማገናዘብ ምላሽ የሚሰጥበት ህክምና ነው። በዚህም ታካሚውና ቤተሰቡ በህመም ሂደት ውስጥ የሚያጋጥማቸውን ጫና ለመቀነስና የኑሮ ጥራታቸውን ለማሻሻል ያግዛል ማለት ነው።
በስልጠናው ላይ የህመም ምንነትና አይነቶች፣ የህመም መጠንን መመዘንና መከታተል፣ የህመም ማስታገሻ ዘዴዎች፣ የታካሚዎችን ስቃይ ለመቀነስ የሚያግዙ የእንክብካቤ አማራጮች፣ የታካሚና የቤተሰብ ድጋፍ እንዲሁም የፓሊያቲቭ ኬር መርሆዎች በስፋት ተዳስሰዋል።

“ህመምን ማከም ብቻ ሳይሆን፤ ስቃይን ማስታገስ፣ ሰውን መንከባከብ እና የኑሮ ጥራትን ማሻሻል—የተሟላ የጤና አገልግሎት መሠረት ነው።”

አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለፋርማሲ አገልግሎት ጥራት እስከ 40 በመቶ በጀት በመመደብ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ነውአዲስ አበባ — ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም.የታካሚ ደኅንነትን...
29/08/2026

አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለፋርማሲ አገልግሎት ጥራት እስከ 40 በመቶ በጀት በመመደብ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ነው
አዲስ አበባ — ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም.
የታካሚ ደኅንነትን፣ የመድኃኒት ጥራትንና ተገቢ አጠቃቀምን ለማረጋገጥ የፋርማሲ አገልግሎት ወሳኝ መሆኑን በመገንዘብ አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለዘርፉ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን ገለጸ።
ሆስፒታሉ ለመድኃኒትና ሕክምና አስተዳደር ኮሚቴ (DTC) አባላት በአዳማ ከተማ ያዘጋጀው የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና የመድኃኒት አጠቃቀምን ይበልጥ ምክንያታዊና ደህንነቱ የተጠበቀ ለማድረግ፣ የመድኃኒት አቅርቦትን ለማጠናከር እና የጎንዮሽ ጉዳት ክትትልን (ADR Monitoring) በብቃት ለመተግበር ያለመ ነው።
የሆስፒታሉ ዋና ዳይሬክተር አቶ ኢዳኦ ፈጆ ስልጠናውን በይፋ በከፈቱበት ወቅት የሕክምና አገልግሎቱን ዓለም ከደረሰበት ደረጃ ለማድረስ የመድኃኒትና የሕክምና መሣሪያዎች ጥራት፣ ተገቢ አጠቃቀም፣ ቀጣይነት ያለው አቅርቦትና ጥብቅ የቁጥጥር ሥርዓት ወሳኝ መሆናቸውን አመላክተዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘውም ሆስፒታሉ ከሚጠቀመው ጠቅላላ በጀት እስከ 40 በመቶ የሚሆነውን ለፋርማሲ አገልግሎት በመመደብ የዘርፉን ጥራትና ተደራሽነት ለማሻሻል ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም ሆስፒታሉ የመድኃኒት ፍላጎትን ከአቅርቦት ጋር በማጣጣም፣ የመድኃኒት አጠቃቀምን በመቆጣጠር እና የመረጃ አያያዝን ዲጂታላይዝድ በማድረግ የፋርማሲ አገልግሎቱን ውጤታማና ቀልጣፋ ለማድረግ የሚከተለውን አቅጣጫ ያመላክታል።
የሆስፒታሉ የፋርማሲ ዳይሬክተር አቶ አበራ ገላን በበኩላቸው የስልጠናው ዋና ዓላማ የመድኃኒት አጠቃቀም ሥርዓትን በዘላቂነት ማስፈን፣ ጊዜያቸው ያለፈባቸውን መድኃኒቶች በስታንዳርዱና በመመሪያ መሠረት በወቅቱ እንዲወገዱ የሚያስችል አሠራር መዘርጋት እንዲሁም የመድኃኒት አቅርቦትን ከዘመናዊ የሕክምና አሠራር ጋር ማጣጣም መሆኑን አስረድተዋል።
“የመድኃኒት ጥራት ማለት የታካሚ ደኅንነት ማለት ነው” በሚል መርህ የDTC አባላት ትክክለኛና ምክንያታዊ የመድኃኒት አጠቃቀምን ስልታዊና ዘላቂ ለማድረግ ጠንካራ የአስተዳደርና የቁጥጥር ሥርዓት በመዘርጋት ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው በስልጠናው ተጠቁሟል።
በተጨማሪም ተገቢ ያልሆነ የመድኃኒት አጠቃቀም በታካሚዎች ላይ ሊያስከትል የሚችለውን አላስፈላጊ ጉዳት መቀነስ፣ የሕክምና ወጪን መቆጣጠር፣ የሕክምና ውጤትን ማሻሻል እና ከእያንዳንዱ የሚሰጥ መድኃኒት ከፍተኛውን የጤና ጥቅም ማረጋገጥ ለታካሚ ደኅንነት ወሳኝ መሆኑ ተመላክቷል።
በመሆኑም አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የፋርማሲ አገልግሎቱን ከመድኃኒት አቅርቦት ባሻገር ከታካሚ ደኅንነት፣ ከሕክምና ጥራትና ከተቋማዊ የጤና አገልግሎት ውጤታማነት ጋር በማስተሳሰር ለማጠናከር እየሠራ መሆኑ ተገልጿል።

አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለአዲስ ገቢ የነርሲንግና የሳይካትሪ ባለሙያዎች የሥራ ላይ ትውውቅና ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ“ጥራት ያለው የአእምሮ ጤና እንክብካቤ የሚጀምረው በ...
28/08/2026

አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለአዲስ ገቢ የነርሲንግና የሳይካትሪ ባለሙያዎች የሥራ ላይ ትውውቅና ግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ
“ጥራት ያለው የአእምሮ ጤና እንክብካቤ የሚጀምረው በተዘጋጀና በሙያው የበቃ ባለሙያ ነው”
አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. – አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አዲስ የተቀላቀሉ የነርሲንግና የሳይካትሪ ባለሙያዎች ከሆስፒታሉ የሥራ ባህል፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓትና ሙያዊ ኃላፊነት ጋር በተግባር እንዲተዋወቁ ያለመ የሥራ ላይ ትውውቅና ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ሰጠ።
ሥልጠናው ከነሐሴ 21 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በሆስፒታሉ የነርሲንግና ሚድዋይፈሪ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ ሲሆን ባለሙያዎቹ የሆስፒታሉን የሥራ አካባቢ በቅርበት እንዲረዱ፣ ተቋማዊ እሴቶችን እንዲጋሩ እና በሳይካትሪ ሕክምናና በአጠቃላይ የነርሲንግ አገልግሎት ዙሪያ የሚተገበሩ ዘመናዊ የሕክምና ፕሮቶኮሎችን እንዲላመዱ ዕድል የፈጠረ ነው።
የአንድ የጤና ባለሙያ ወደ ሥራ መግባት የሙያ ተግባርን መጀመር ብቻ አይደለም፤ የታካሚን ሕይወት፣ ክብርና ተስፋ የመጠበቅ ኃላፊነትን መሸከምም ነው። በተለይ በአእምሮ ጤና አገልግሎት ይህ ኃላፊነት የበለጠ የላቀ ሙያዊ ብቃትን፣ ትዕግሥትንና ሰብዓዊ አቀራረብን ይጠይቃል።
በሥልጠናው ወቅት አዲስ ገቢ ባለሙያዎቹ ከሆስፒታሉ አስተዳደራዊ መዋቅርና የሥራ አሠራር ጋር ከመተዋወቅ ባሻገር የታካሚ እንክብካቤ፣ የሙያ ሥነ-ምግባር፣ የታካሚ ደህንነት፣ የድንገተኛና የመደበኛ የሕክምና ፕሮቶኮሎች አተገባበር እና የቡድን ሥራ ዙሪያ ጠቃሚ ግንዛቤዎችን አግኝተዋል።
የሥልጠናው ዋና ዓላማም አዲስ ገቢ ባለሙያዎቹ ከተቋሙ የሥራ ባህል ጋር በፍጥነት እንዲዋሃዱ፣ የሙያ ኃላፊነታቸውን በተሟላ ሁኔታ እንዲወጡ እና በየክፍሉ የሚተገበሩ የሕክምናና የነርሲንግ ፕሮቶኮሎችን በጥብቅ በመከተል የተሻለ የታካሚ እንክብካቤ እንዲሰጡ ማስቻል ነው።
ባለሙያዎቹ በሥልጠናው ያገኙት ተግባራዊና ንድፈ-ሐሳባዊ ዕውቀት በሆስፒታሉ የስራ ቆይታቸው ለሚኖራቸው ሙያዊ ኃላፊነት ጠንካራ መሠረት እንደሚያስገኝላቸው ይጠበቃል። በተለይም ታካሚን በክብርና በርኅራኄ መንከባከብ፣ የሙያ ሥነ-ምግባርን መጠበቅ እና የሕክምና ፕሮቶኮሎችን በትክክል መተግበር ላይ የሚኖራቸውን ግንዛቤ ይበልጥ ያጠናክራል።
በአእምሮ ጤና አገልግሎት ውስጥ ታካሚዎች ልዩ የሆነ ሙያዊ እንክብካቤን፣ ትዕግሥትን፣ ርኅራኄንና የሙያ ሥነ-ምግባርን የሚጠይቅ አገልግሎት እንደሚፈልጉ በመገንዘብ የሥራ ላይ ትውውቅና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎች ለባለሙያዎች የሥራ ዝግጁነትን ከማሳደግ ባሻገር የታካሚ ደህንነትንና የአገልግሎት ጥራትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና አለው።
በመጨረሻም ሆስፒታሉ የአእምሮ ጤናና አጠቃላይ የጤና አገልግሎት ጥራትን በቀጣይነት ለማሻሻል ብቁና ተነሳሽነት ያላቸው የጤና ባለሙያዎችን ማብቃትና ማስተዋወቅ ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራ አመላክቷል።

24/08/2026
ጤናን በመናገር ብቻ ሳይሆን በመኖር! — አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሰራተኞች በRC76 “Walk the Talk” ተሳትፎአዲስ አበባ — ነሐሴ 17/ 2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ...
23/08/2026

ጤናን በመናገር ብቻ ሳይሆን በመኖር! — አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሰራተኞች በRC76 “Walk the Talk” ተሳትፎ
አዲስ አበባ — ነሐሴ 17/ 2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)
አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአመራር አካላትና ሰራተኞች በ76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የክልል ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) አካል በተዘጋጀው “Walk the Talk” የእግር ጉዞ መርሃ ግብር ላይ በንቃት ተሳትፈዋል።
76ኛው የዓለም ጤና ድርጅት የክልል ኮሚቴ ስብሰባ (RC76) ከነሐሴ 17–22 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን በስብሰባው የጤና ሥርዓትን ማጠናከር፣ የጤና ልማትን ማስፋፋት እና ለህዝቦች የተሻለ የጤና አገልግሎት ማረጋገጥን የሚመለከቱ የተለያዩ አጀንዳዎች የሚመከሩበት እነደሚሆን ይታመናል።
በአጀንዳው ከተካተቱ የጤና ማስፋፊያ እንቅስቃሴዎች መካከል “Walk the Talk” የእግር ጉዞ መርሃ ግብር አንዱ ሲሆን የመርሃ ግብሩ ዋና ዓላማ ሰዎች በየዕለቱ አካላዊ እንቅስቃሴን የሕይወታቸው አካል እንዲያደርጉ ማበረታታት፣ ጤናማ አኗኗርን ማስፋፋት እና በተግባር የጤና መልዕክትን ማስተላለፍ ነው።
በዚህ መርሃ ግብር አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አመራርና ሰራተኞች መሳተፋቸው የአካል ጤናና የአእምሮ ጤና በአንድነት የሚታዩ እሴቶች መሆናቸውን ያሳዩበት ሆኗል።
መርሃ ግብሩ ከአካላዊ እንቅስቃሴና ከጤናማ አኗኗር ማበረታታት ባሻገር አዲስ አበባ እያከናወነች ያለችውን የከተማ ልማት ለዓለም አቀፍ ተሳታፊዎች ለማስተዋወቅም ዕድል ፈጥሯል። ተሳታፊዎች በእግር ጉዞው ወቅት የከተማዋን የኮሪደር ልማት፣ አረንጓዴ መሠረተ ልማቶችን፣ የሕዝብ መዝናኛና የእግረኛ መንገዶችን እንዲሁም የአዲስ አበባን ታሪካዊና ባህላዊ ሀብቶች በመመልከት የከተማዋን የልማት ገጽታ ለመመልከት ችለዋል።
የኮሪደር ልማትና አረንጓዴ መሠረተ ልማት ከከተማ ውበት በላይ ለሕዝብ ጤና የሚኖራቸው አስተዋፅዖ ከፍተኛ ነው። የእግረኛ መንገዶች፣ አረንጓዴ ስፍራዎችና ለአካላዊ እንቅስቃሴ ምቹ የሆኑ የከተማ አካባቢዎች ሰዎች በእግር እንዲጓዙ፣ እንዲያርፉና አካላዊ እንቅስቃሴ እንዲያዘወትሩ የሚያበረታቱ ሲሆን፣ ይህም በአካልና በአእምሮ ጤና ላይ ጠቃሚ ተፅዕኖ ያሳድራል።
የአእምሮ ጤና ከአካላዊ ጤና ተለይቶ የሚታይ ጉዳይ ሳይሆን ከአኗኗር፣ ከአካላዊ እንቅስቃሴ፣ ከማህበራዊ ተሳትፎና ከጤናማ አካባቢ ጋር የሚተሳሰር የጤና ጉዳይ ነው።

“ጤናን በመናገር ብቻ ሳይሆን በመኖር እንመስክር!”

የሐዘን መግለጫበአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች ሲያገለግሉ የነበሩትና እስከ ሕይወታቸው ማለፊያ ድረስ የአቤት ሆስፒታል ዋና ሥራ አስፈጻሚ (CEO) በመ...
19/08/2026

የሐዘን መግለጫ
በአለርት ኮምፕርሄንሲቭ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በተለያዩ የሥራ ኃላፊነቶች ሲያገለግሉ የነበሩትና እስከ ሕይወታቸው ማለፊያ ድረስ የአቤት ሆስፒታል ዋና ሥራ አስፈጻሚ (CEO) በመሆን ያገለገሉት ዶ/ር ጸጋዬ ገብረ አናንያ በገጠማቸው ድንገተኛ ህልፈተ ህይወት የሆስፒታሉ አመራሮችና ሠራተኞች የተሰማንን እጅግ ከፍተኛ ሀዘን እየገፅለን ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጆቻቸውና ለስራ ባልደረቦቻቸው ሁሉ ፈጣሪ መፅናናትን ያድልልን ዘንድ እንመኛለን።

አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል

አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአገልግሎት ጥራትን በዘላቂነት ለማሻሻል ያለመ የንድፈ-ሃሳብና የተግባር ስልጠና ሰጠአዲስ አበባ፦ ነሐሴ 9 ቀን 2018 ዓ.ም.አማኑኤል የአእምሮ ስፔ...
16/08/2026

አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአገልግሎት ጥራትን በዘላቂነት ለማሻሻል ያለመ የንድፈ-ሃሳብና የተግባር ስልጠና ሰጠ
አዲስ አበባ፦ ነሐሴ 9 ቀን 2018 ዓ.ም.
አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የአእምሮ ጤና ሕክምና አገልግሎትን ጥራት በዘላቂነት ለማሻሻል ያለመ የንድፈ ሐሳብና የተግባር የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ለጤና ባለሙያዎች ሰጠ።
ስልጠናው ከነሐሴ 7 እስከ 9 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዳማ ከተማ የተካሄደ ሲሆን በሕክምና ጥራት ማሻሻያ ስታንዳርዶችና በጥራት ማሻሻያ (Quality Improvement) አሰራሮች ላይ ትኩረት አድርጓል።
የስልጠናው ዋና ዓላማ የአእምሮ ጤና አገልግሎትን ዘመናዊ የሕክምና አሰራሮችንና የጥራት ደረጃዎችን በመተግበር ማሻሻል፣ የሕክምና አገልግሎቱ አገር አቀፍና ዓለም አቀፍ የጥራት መስፈርቶችን እንዲያሟላ ማስቻል እና በአገልግሎት አሰጣጥ የሚታዩ ክፍተቶችን በመለየት ውጤታማ የማሻሻያ ርምጃዎችን መተግበር ላይ ያለመ ነው።
በዚህም የጥራት ማሻሻያ ሞዴሎችን በመጠቀም ችግሮችን በማስረጃ ላይ ተመስርቶ መለየት፣ ተገቢ የማሻሻያ ጣልቃ-ገብነቶችን መንደፍና መተግበር እንዲሁም የተገልጋዮችን እርካታና የተቋሙን አፈጻጸም ማሻሻል ላይ በማተኮር ስልጠናው ተሰጥቷል።
የሆስፒታሉ የጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ መኮንን አስፋው ስልጠናው የታካሚዎችን የሕክምና ውጤት ለማሻሻልና የሆስፒታሉን አገልግሎቶች ብሔራዊና ዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃዎችን አሟልተው ለመተግበር የሚያስችል ከፍተኛ ፋይዳ ያለው መሆኑን ገልፀዋል።
የስነ-አእምሮ ሕክምና ዳይሬክተር ዶ/ር ሉሉ በቃና በበኩላቸው ሆስፒታሉ ተወዳዳሪና ተመራጭ የአእምሮ ጤና ተቋም ሆኖ እንዲቀጥል የጥራት ማሻሻያ ሥራዎችን በተጠናከረ መልኩ መቀጠል እንደሚገባ ገልጸዋል።
ዶ/ር ሉሉ አክለውም በጥራት ማሻሻያ ደረጃዎች ላይ የተመሠረተ ለውጥ፣ የባለሙያዎች ቁርጠኝነት፣ የቡድን መንፈስና ቅንጅታዊ አሠራር ለሁለንተናዊ ተቋማዊ ግንባታና ለዘላቂ የአገልግሎት ጥራት ማሻሻያ ወሳኝ መሆናቸውን አስገንዝበዋል።
በመጨረሻም የጤና ባለሙያዎች በሙያቸው ወቅታዊ የሆኑ እውቀትና ክህሎቶችን በቀጣይነት በማዳበር፣ ለማህበረሰቡ ጥራት ያለው፣ ተደራሽና ታካሚ-ተኮር የአእምሮ ጤና አገልግሎት ማቅረብ እንዳለባቸው ተጠቁሟል።
ለዚህም አስፈላጊ የሆኑ የሰው ኃይል አቅም ግንባታና የሙያ ማሻሻያ ሥራዎች በቀጣይነት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተገልጿል።

አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀሙን ገመገመ፤ የማስፋፊያ ግንባታ የቦታ ርክክብ ሂደት ላይ መሆኑ ተገለጸአዲስ አበባ ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስ...
14/08/2026

አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት አፈፃፀሙን ገመገመ፤ የማስፋፊያ ግንባታ የቦታ ርክክብ ሂደት ላይ መሆኑ ተገለጸ
አዲስ አበባ ሐምሌ 7/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)
​አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የ2018 በጀት ዓመት አራተኛ ሩብ ዓመት አፈፃፀሙንና ያጋጠሙትን ተግዳሮቶች አስመልክቶ ከማህበረሰብ ተወካዮች ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ። በውይይት መድረኩ ላይ የሆስፒታሉ አመራሮች እና የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች የተገኙ ሲሆን ዋና ዓላማውም ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚቀርቡ የአገልግሎት አሰጣጥ ግብረመልሶች ላይ በመመርኮዝ የሕክምና አገልግሎት ጥራትንና ተደራሽነትን ማሻሻል እንዲሁም የታካሚዎችን እርካታ ማረጋገጥ እንደሆነ ተገልጿል።
​በግምገማ መድረኩ ባለፉት 12 ወራት ውስጥ የተመዘገቡ አዎንታዊ ለውጦች፣ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እና በቀጣይ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ላይ ጥልቅ ውይይት ተደርጓል። በውይይቱ የአእምሮ ጤና መድኃኒቶችን አቅርቦት ለማሻሻል ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸው ተገልጿል። ይሁን እንጂ ተጨማሪ ቅርንጫፎችን በመክፈት መድኃኒቶችን በስፋት ለማዳረስ የቦታ እጥረት እና የቤት ኪራይ ዋጋ መናር ተግዳሮት እንደሆኑ ተመላክቷል።
በሌላ በኩል በሁሉም የህክምና አገልግሎት መስጫ ክፍሎች ወረቀት አልባ የሆነ የኤሌክትሮኒክስ የሕክምና ምዝገባና የመረጃ አያያዝ ሥርዓት (EMR) አጠናክሮ በማስቀጠል የህክምና አገልግሎቱን አሰጣጡን የተቀላጠፈና ዘመናዊ በማድረግ የጤና ዲጂታላይዜሽን ስራዎችን አጠናክሮ በማስቀጠል ከፍተኛ ሚና እየተጫዎተ እንደሚገኝ ተገልጿል። በተጨማሪም ሆስፒታሉ ከአእምሮ ህመም ሕክምና አገልግሎት ጎን ለጎን አዳዲስ የሕክምናና የምርመራ አገልግሎቶችን ማስጀመሩ ተብራርቷል።
​በውይይቱ ከተነሱ ዋና ዋና ማነቆዎች መካከል የቦታ ጥበት እና የመሠረተ ልማት ችግሮች ለተቋሙ አገልግሎት መስጠት ፈተና ሆነው መቆየታቸው ተነስቷል። ይህንን የረጅም ጊዜ ችግር በዘላቂነት ለመፍታትም ለሆስፒታሉ ማስፋፊያ የሚሆን ቦታ በሚመለከተው አካል ተፈቅዶ አዲስ የማስፋፊያ ግንባታ ለማከናወን የቦታ ርክክብ ሂደት ላይ የሚገኝ መሆኑም ተመላክቷል።
​የማህበረሰብ ተወካዮች በበኩላቸው ሆስፒታሉ እየሰጠ ባለው አገልግሎት እና ለችግሮች የመፍትሄ አቅጣጫዎችን በመንደፍ ከህብረተሰቡ ጋር በቅርበት መስራቱ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ገልፀው ሆስፒታሉ በአእምሮ ጤና አገልግሎት ጥራቱንና ተደራሽነቱን የጠበቀ የህክምና አገልግሎት ለመስጠት የሚያደርገውን ጥረት ለማገዝ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
​በመጨረሻም ከማህበረሰብ ተወካዮች የተገኙ ገንቢ አስተያየቶች ተቀምረው ለ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ እንደ ግብአት እንደሚወሰዱ እና ሆስፒታሉን የላቀ የሕክምና ማዕከል ለማድረግ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ በአፅንኦት ተመላክቷል።

ለዜጎች ሁለንተናዊ ፈውስ ዛሬን እንትከል!​አዲስ አበባ፦ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በምዕራብ ሸዋ ዞን የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር...
06/08/2026

ለዜጎች ሁለንተናዊ ፈውስ ዛሬን እንትከል!
​አዲስ አበባ፦ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)
አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በምዕራብ ሸዋ ዞን የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደ።
​"ጤናማ አእምሮ በለም አካባቢ ይለመልማል" በሚል መሪ ቃል አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ኤጀሬ ከተማ በ1.3 ሄክታር መሬት ላይ 5,000 ችግኞችን በመትከል አሻራውን አሳርፏል።
​በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብሩ ላይ የአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የበጎ ፈቃድ ስራ ወጣቶች፣ የኤጀሬ ከተማ አስተዳደር አመራሮች እንዲሁም የኤጀሬ ከተማ ከንቲባ በቦታው በመገኘት ችግኞችን በጋራ በመትከል የመርሃ ግብሩ ተሳታፊ ሆነዋል።
​የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች እንደገለጹት የተተከሉት ችግኞች ከሚሰጡት አጠቃላይ ሃገራዊ ጠቀሜታ ባለፈ ከፍተኛ ማህበረሰባዊ ቁርኝትና ትስስር የፈጠረ ነው ብለዋል።
​ሆስፒታሉ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ በኤጀሬ ከተማ በቋሚነት የተለያዩ ሃገር በቀል ችግኞችን ሲተከል የቆየ ሲሆን አካባቢውን አረንጓዴ በማልበስ የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትላቸውን ተፅዕኖዎች በመከላከል ላይ ይገኛል። "ጤናማ አእምሮ በለም አካባቢ" እንደሚለመልመው ሁሉ ለምለምና የተፈጥሮ ጸጋ የተሞላበት አካባቢ ለዜጎች ሁለንተናዊ የአእምሮና የአካል ጤና ፈውስ በመፍጠር እንዲሁም ለአካባቢው ማህበረሰብ ለምግብነት እና ለመድሃኒትነት አገልግሎት የሚውሉ የዛፍ ችግኞች መካተታቸው ደግሞ ጠቀሜታውን ከፍ ለማድረግ ያለመ መሆኑ ተመላክቷል።
​የሰው ልጅ ከዕለት ወደ ዕለት ከሚያጋጥሙት ፈተናዎች መካከል የአየር ንብረት ለውጥ፣ የሀብት መመናመን እና የስነ-ምህዳር መዛባት ግንባር ቀደሞቹ ናቸው። ኢትዮጵያ ይህንን ዓለም አቀፍ ችግር በግንባር ቀደምነት ለመቋቋም ከቀረፀቻቸው ስትራቴጂካዊ እርምጃዎች መካከል «የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር» ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል። ይህ መርሃ ግብር የነገውን ትውልድ ደህንነት ለመጠበቅ ዛሬ የሚቀመጥ ቋሚ ማዕዘን ነው።
​በመሆኑም ጤናማ ማህበረሰብን ለመገንባት የሕክምና አገልግሎት ብቻውን በቂ እንዳልሆነ የተገነዘበው አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ከህክምና አገልግሎቱ ጎን ለጎን እንዲህ ያሉ ማህበራዊ ኃላፊነትና የአካባቢ ጥበቃ ስራዎችን አጠናክሮ እየሰራ ይገኛል፡፡ ሆስፒታሉ ጤናማ ማህበረሰብ እንዲኖር ጤናማ አካባቢ አስፈላጊ ነው ብሎም ያምናል።
​በዚህም መሰረት ሆስፒታሉ በመጀመሪያው ምዕራፍ (ከ2015 ጀምሮ ለ3 ተከታታይ ዓመታት)፦ በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ኤጀሬ ከተማ ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በመቀናጀት በ50,000 ካሬ ሜትር መሬት ላይ 20,000 ለምግብነትና ለመድሃኒትነት የሚውሉ ሀገር በቀል የዛፍ ችግኞችን በማልማትና በመትከል የአየር ንብረት ፅናትን በማስጠበቁ ሂደት የበኩሉን ድርሻ አበርክቷል።
በአሁኑ ምዕራፍ (በ2018 ክረምት) ደግሞ እንደ ሀገር በአንድ ጀንበር 800 ሚሊዮን ችግኞችን የመትከል ግብን ለማሳካት በተያዘው ኢኒሼቲቭ ሆስፒታሉ በአራተኛው ዙሩ 5,000 ሀገር በቀል ለምግብነትና ለመድሃኒትነት አገልግሎት የሚሰጡ ችግኞችን በኤጀሬ ከተማ በ1.3 ሄክታር መሬት ላይ በመትከል ለትውልድ ተሻጋሪ የሆነ አሻራውን አሳርፏል።
​ይህ ተግባር ሆስፒታሉ የማህበረሰብን አዕምሯዊ ጤና ከመጠበቅ ባሻገር የስነ-ምህዳር ሚዛንን በመጠበቅ በኩል ያለውን ከፍተኛ ኃላፊነት በግንባር ቀደምትነት ያሳየበት እና ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ልማት ሉዓላዊት ሃገር የመሆን ራዕይዋ እንዲሳካ የበኩሉን አሻራ ያሳረፈበት ድንቅ ምዕራፍ ነው።
​የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የነገዋን ኢትዮጵያ ገጽታ የሚወስን ታላቅ ሀገራዊ ራዕይ ነው። በመሆኑም እንደ አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ያሉ ተቋማት ከዕለት የዕለት የስራ አፈፃፀማቸው ባለፈ ለአካባቢና ስነምህዳር ደህንነት የሚያደርጉት አስተዋጽኦ የጋራ ሀገራዊ ግቦችን ለማሳካት ቁልፍ ሚና ያለው ሲሆን የዛሬው ትብብርና ትጋት ለነገው ትውልድ የሚተላለፍ የህይወት ውርስ ነው።

የጤና ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 30 ሺህ ችግኞችን ተከሉ።​አዲስ አበባ - ሐምሌ 27/ 2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)​"ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ...
03/08/2026

የጤና ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት በአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 30 ሺህ ችግኞችን ተከሉ።
​አዲስ አበባ - ሐምሌ 27/ 2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)
​"ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ሀሳብ ሀገር አቀፍ አጠቃላይ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር አስመልክቶ በተከናወነው በአንድ ጀንበር 800 ሚሊዮን ችግኝ የመትከል ኘሮግራም ላይ የጤና ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች፣ የፌዴራል ሆስፒታሎች፣ ተጠሪ ተቋማት፥ ኤጀንሲዎች የማኔጅመንት አባላት እንዲሁም የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባላት በጋራ በመሆን በሸገር አስተዳደር በገፈርሳ ጉጄ ክፍለ ከተማ በገፈርሳ ሀይቅ አካባቢ ችግኞችን ተከሉ።
​በጤናው ዘርፍ በ2018 ክረምት ወራት 250 ሺህ ችግኞችን ለመትከል በዕቅድ ተይዞ እየተሠራ የሚገኝ ሲሆን በዕለቱም በተከናወነው ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ 30 ሺህ ችግኞችን መትከል ተችሏል።
​በመርሃ ግብሩ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የጤና ሚኒስትር ክብርት ዶ/ር መቅደስ ዳባ "እጃችን ሥራ ሰርቶ ለትውልድ አሻራ የምናስቀምጥበት ዕለት እንኳን አደረሳችሁ" ብለዋል። አያይዘውም ሀገራችን በነፃነት ሉዓላዊነቷን አረጋግጣ እንደቆየችው ሁሉ በአረንጓዴ አሻራም የሁልጊዜም ሉዓላዊት ሀገር እንድትሆን እንሰራለን ሲሉ በአጽንኦት ሰጥተው ተናግረዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ዶ/ር ደረጀ ደጉማ በበኩላቸው "ጤናና ችግኝ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታዎች ናቸው" ያሉ ሲሆን ችግኝን መትከል የምንተነፍሰውን አየር፣ የምንመገበውን ምግብ እንዲሁም የሕክምና መሰረት የሆነውን መድሃኒታችንን ማምረት መቻል ነው ብለዋል።
በዚህ ታላቅ የህዝብ ተሳትፎ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የጤና ሚ/ር ከፍተኛ ባለስልጣናት ፥ የማኔጅመንት አባላት እና የሃገር መከላከያ ሠራዊት አባላት አረንጓዴ ልማቱ የነገን ትውልድ ደህንነት እና የስነምህዳር ጽኑ መሰረት የሚጥል መሆኑን ገልጸው በቀጣይም የተተከሉትን በመንከባከብ የነቃ ተሳትፏቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።

Address

Addis Ababa Ethiopia Addis Ketema Subcity At The Vicinity Of Mesalemeya
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Amanuel mental specialized hospital posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share