21/05/2026
በድንገተኛና ወሳኝ ክብካቤ ላይ ያተኮረ የፅንሰ-ሃሳብና የተግባር ስልጠና ተሰጠ
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 13/2018 ዓ.ም (አማ/አእ/ስፔ/ሆ/ል)፦ አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ለጤና ባለሙያዎቹ ያዘጋጀው በድንገተኛና ወሳኝ እንክብካቤ አያያዝና አተገባበር ላይ ያተኮረ የፅንሰ-ሃሳብና የተግባር ስልጠና በአዳማ ከተማ ሰጠ።
ከግንቦት 10 እስከ 13/2018 ዓ.ም ድረስ በተሰጠው በዚህ ስልጠና ላይ ከሆስፒታሉ የተውጣጡ የጤና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል። በስልጠናው መክፈቻ ላይ የድንገተኛ ህክምና ዲፖርትመንት ሃላፊ የሆኑት ዶ/ር ሚክያስ ጥላሁን እንደተናገሩት ድንገተኛ አደጋዎች አስቀድመው አይቀጠሩም። የአየር መተላለፊያ መዘጋት፣ ድንገተኛ የልብ መቆም፣ የደም ግፊትና የደም ዝውውር መዛባት በማንኛውም ሰዓትና ቦታ ሊያጋጥሙ የሚችሉ ስጋቶች ናቸው። በእንዲህ አይነት አስጨናቂ እና በሕይወትና በሞት መካከል ባሉ ደቂቃዎች ውስጥ ልዩነቱን የሚፈጥረው የሕክምና መሣሪያው መኖር ብቻ ሳይሆን መሣሪያውን በልበ-ሙሉነትና በጥራት መጠቀም የሚችል የሰለጠነ የሰው ኃይል መኖሩ ነው።
ለዚህም ነው ይህንን ሥልጠና እጅግ አስፈላጊና ወቅታዊ የሚያደርገው በማለት ተናግረዋል።
የሆስፒታሉ የፅ/ቤት ሃላፊ አቶ መኮንን አስፋው በበኩላቸው አማኑኤል የአእምሮ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በአገሪቱ የአእምሮ ጤና ሕክምና ላይ ግንባር ቀደም ተቋም መሆኑ ይታወቃል። ሆኖም የአእምሮ ጤና እክሎችና ሕክምናዎች በራሳቸው ከተለያዩ ድንገተኛና አፋጣኝ የውስጥ ደዌ ወይም የአካል ጉዳት አደጋዎች ጋር የመገናኘት ዕድላቸው ሰፊ ነው በመሆኑም ማንኛውም ታካሚ ወደ ተቋማችን ሲመጣ የአእምሮ ጤና ድጋፍ ብቻ ሳይሆን ሙሉና አስተማማኝ የሕክምና ዋስትና የመሻት መብት ስላለው ሆስፒታሉ በሰው ሃይልና በህክምና ቁሳቁስ የመደገፍና የማጠናከር ስራዎችን እንደሚሰራ ገልፀዋል።
ስልጠናው በዋናነት ባለሙያዎቹ ድንገተኛና አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ለሚያስፈልጋቸው ታካሚዎች የሚሰጡትን ምላሽ ይበልጥ ፈጣን፣ ስልታዊና ሳይንሳዊ ለማድረግ የታለመ ሲሆን
የአደጋ ጊዜ ታካሚዎችን ሁኔታ በፍጥነት መገምገምና የደም ዝውውር መዛባትን በፈጣን ህክምና ማረጋጋት፤ የመተንፈሻ አካል ችግር ላጋጠማቸው ታካሚዎች የላቀ የአየር መተላለፊያ መክፈቻ ዘዴዎችን መጠቀምና በመተንፈሻ መሳሪያ መደገፍ፤ መሰረታዊ የህይወት ድጋፍ ፣ የላቀ የልብና የደም ቧንቧ ህይወት ድጋፍ እንዲሁም አውቶማቲክ ውጫዊ ዲፊብሪሌተር (AED) መሳሪያን በመጠቀም የልብና የመተንፈስ ችግር ያጋጠማቸውን ታካሚዎች ህይወት ማዳን ላይ ትኩረት አድርጎ ተሰጥቷል። በተጨማሪም የስኳር በሽታ ኬቶአሲዶሲስ እና ሃይፐርኦስሞላር ሃይፐርግሊሴሚክ ሁኔታ ማለትም ከፍተኛ የሆነ የደም ስኳር መጠን መጨመር የሚያስከትሏቸው እና አስቸኳይ ህክምና የሚያስፈልጋቸው አደገኛ የስኳር በሽታ ውስብስብ ችግሮች ላይ ምልክቶችን ተረድቶ ስለሚደረግ አፋጣኝ የህክምና እርዳታ የስልጠናው አካል ተደርጓል።
ስልጠናው ባለሙያዎቹ ያላቸውን የንድፈ-ሃሳብ እውቀት በተግባራዊ ልምምድ እንዲያበለጽጉ ያስቻለ ሲሆን በሆስፒታሉ የሚሰጠውን የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ጥራትና ዝግጁነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለውም ተገልጿል።
conceptual andppractical trainingon eemergencyand ccritical care providedAddis Ababa; May 13/2018 E.c (EMSH): Emmanuel Mental Specialized Hospital provided a concept and practical training on emergency and critical care management and implementation for its health professionals in Adama city.
Health professionals from the hospital participated in this training, which was given from May 10 to 13/2018 E.c. At the opening of the training, Dr. Mikyas Tilahun, Head of the Emergency Department, said that emergencies are not planned in advance. Airway obstruction, sudden cardiac arrest, blood pressure and circulatory disorders are threats that can occur at any time and place. In such a stressful and life-and-death situation, the difference is not only in the availability of medical equipment, but also in the availability of trained personnel who can use the equipment with completeness and quality.
That is why he said that this training is very important and timely.
The hospital’s cchiefof sstaff,Ato Mekonnen Asfaw, for his part, said that Emmanuel Mental Specialized Hospital is known to be a leading hospital in mental health treatment in the country. However, mental health disorders and treatments themselves have a high chance of being associated with various sudden and urgent internal diseases or physical injuries. Therefore, when any patient comes to our hospital, he said that he has the right to seek not only mental health support but also complete and reliable medical care, so the hospital will work to support and strengthen it with human resources and medical equipment.
The training is primarily aimed at making the response of professionals to patients in need of emergency and urgent medical care more rapid, systematic and scientific.
Rapid assessment of emergency patients and stabilization of circulatory disorders with rapid ttreatment,use of advanced airway management and ventilator support for patients with respiratory pproblems,basic life support, advanced cardiovascular life ssupport, and the use of automated external defibrillator (AED) devices were focused on saving the lives of patients with cardiac and respiratory problems. In addition, the training focused on understanding the symptoms of diabetic ketoacidosis and hyperosmolar hyperglycemic state, which are dangerous complications of diabetes that cause high blood sugar levels and require urgent treatment.
The training has enabled the professionals to enrich their theoretical knowledge with practical experience and has contributed significantly to improving the quality and preparedness of emergency medical services provided at the hospital.