Yekatit 12 Hospital Medical College

Yekatit 12 Hospital Medical College Yekatit 12 Hospital was founded in 1923 and one of the 1st modern hospitals in the country.

Yekatit 12 Hospital started providing medical education in 2011 and changed its name to Yekatit 12 Hospital Medical College.

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በግል ህክምና/private wing ከሚሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች መካከል የውስጥ ደዌ ህክምና ይገኝበታል።በመሆኑም ከሰኔ/1/2018 ዓ.ም ጀምሮ በውስጥ...
05/06/2026

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በግል ህክምና/private wing ከሚሰጣቸው የህክምና አገልግሎቶች መካከል የውስጥ ደዌ ህክምና ይገኝበታል።

በመሆኑም ከሰኔ/1/2018 ዓ.ም ጀምሮ በውስጥ ደዌ ህክምና በሰብ ስፔሻሊስት እና ስፔሻሊስት ሃኪሞች በመታገዝ ደረጃውን የጠበቀ የህክምና አገልግሎት ይሰጣል

ዘውትር ከሰኞ እስከ አርብ ከአመሻሹ 11 ሰዓት ጀምኖ
ዘውትር ቅዳሜ ከጠዋቱ 2:00-6:00 ሰዓት አገልግሎቱን ያገኛሉ።

📚 Empowering Students for Academic Success and Life ReadinessThe Adolescent and Youth Health Service team at Yekatit 12 ...
04/06/2026

📚 Empowering Students for Academic Success and Life Readiness

The Adolescent and Youth Health Service team at Yekatit 12 Hospital Medical College successfully conducted an impactful training program titled “Mastering Memory: The Science of Flawless Study Habits & Life Readiness” for 64 youth group students, just 30 days before their final examinations.

The training was designed to strengthen students’ academic performance while preparing them for the opportunities and challenges that lie ahead in college and the workplace.

During the session, students learned evidence-based study strategies grounded in the Atkinson-Shiffrin Multi-Store Memory Model. Key topics included:

✅ Eliminating digital distractions through the “Zero-Device Zone” approach

✅ Improving focus and information retention using memory chunking techniques

✅ Managing exam stress through the Physiological Sigh breathing method

✅ Strengthening long-term memory through Active Recall, the Blurting Method, and the First-Minute Brain Dump strategy

In addition to academic skills, the program incorporated essential life-readiness interventions, including HIV Counseling and Testing (HCT), health education, and guided discussions on responsible relationships, peer influence, and healthy decision-making during transitions to higher education and future workplaces.

By integrating cognitive science, health awareness, and personal development, the training equipped participants with practical tools to excel academically while making informed choices for their future well-being.

Yekatit 12 Hospital Medical College remains committed to empowering adolescents and youth through comprehensive health promotion, education, and life-skills development initiatives.

📌 Follow Us on Social Media
👉 Facebook:
https://www.facebook.com/profile.php?id=100063650457050

👉 Telegram: Join Our Channel https://t.me/Y12HMCC

👉 Follow us on tiktok
https://vm.tiktok.com/ZMHWJyPGKQmQp-dftjE/

🔖

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በዘመናዊ ቀዶ ጥገና እና በሰብ-ስፔሻላይዜሽን አገልግሎት የላቀ ከፍታ ላይ መድረሱ ተገለጠ #​አዲስ አበባ — የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ባለፉት ...
03/06/2026

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በዘመናዊ ቀዶ ጥገና እና በሰብ-ስፔሻላይዜሽን አገልግሎት የላቀ ከፍታ ላይ መድረሱ ተገለጠ

#​አዲስ አበባ — የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ባለፉት ሁለት ዓመታት ባደረገው ዘርፈ-ብዙ መዋቅራዊ ሪፎርም፣ የሰው ኃይል ልማት እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ራሱን ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ወደ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ደረጃ ማሳደጉን አስታወቀ።

ሜዲካል ኮሌጁ በአሁኑ ወቅት በከተማ አስተዳደሩ ስር ካሉ ተቋማት በላቀ ሁኔታ በሰብ-ስፔሻላይዜሽን (Sub-specialization) ዘርፍ ሰፊና አስደናቂ ስኬቶችን እያስመዘገበ ይገኛል።

​የሆስፒታሉ የቀዶ ህክምና ክፍል ዳይሬክተር ዶ/ር ዳንኤል አበበ እንደገለጹት፤ ተቋሙ በአሁኑ ወቅት ይዘታቸውና አደረጃጀታቸው ዓለም አቀፍ ደረጃን በጠበቁ 13 የተለያዩ የህክምና ክፍሎች (Departments) ተዋቅሮ፣ ለህብረተሰቡ እጅግ ዘመናዊና የተቀናጀ የህክምና አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል።

​ቀደም ባሉት ዓመታት ተቋሙ ትኩረት አድርጎ ይሰራ የነበረው መደበኛ የሆድ ዕቃ ቀዶ ጥገና (General Surgery) ላይ ብቻ እንደነበረ ያስታወሱት ዶ/ር ዳንኤል፣ አሁን ላይ ግን ሆስፒታሉ ሙሉ አቅሙን በማጠናከር ሁሉንም ዓይነት የላቁ የቀዶ ጥገና ዘርፎችን ማካተት መቻሉን አብራርተዋል።

​በተለይም የሐሞት ከረጢት ጠጠር (Cholelithiasis) ህክምናን ጨምሮ አብዛኛዎቹ የሆድ ዕቃ ቀዶ ጥገናዎች ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ በላፓራስኮፒ (በቀዳዳ ቀዶ ጥገና) ዘመናዊ መሣሪያ የታገዙ ሆነዋል። ይህም የታካሚዎችን የመድኃን ጊዜ ያሳጠረና የህክምና ጥራቱን ያሳደገ ትልቅ ስኬት ነው።

በአሁኑ ወቅት ሆስፒታሉ 8 ዋና ዋና (Major) እና 1 አነስተኛ (Minor) የቀዶ ጥገና ክፍሎችን ሙሉ በሙሉ በማደራጀትና አቅማቸውን በአግባቡ በመጠቀም ቀልጣፋ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። እንደ ትርፍ አንጀት (Appendicitis)፣ የሆድ ዕቃ መዘጋት (Bowel Obstruction)፣ አጣዳፊ የሐሞት ከረጢት ህመም (Acute Cholecystitis)፣ የደረት አደጋዎች (Chest Trauma)፣ የማህፀንና የወሊድ ድንገተኛ ቀዶ ጥገና (Gyn/Obs Emergency)፣ የህፃናት ቀዶ ጥገና (Pediatric Surgery)፣ ኦርቶፔዲክስ (Ortho) እና ኒውሮ ሰርጀሪ (Neuro) በከፍተኛ ጥራት እየተሰጡ ይገኛሉ።

በተጨማሪም የጆሮ፣ አፍንጫና ጉሮሮ (ENT)፣ የማክሲሎፌሻል (Maxillofacial)፣ የደም ሥር ቀዶ ጥገና (Vascular) እና የጉበትና የሐሞት ከረጢት (Hepatobiliary) ሰርጀሪዎች በስፋትና በስኬት እየተከናወኑ መሆኑን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

​በሆስፒታሉ የቀዶ ጥገና ክፍል ውስጥ በአንድ ወር ውስጥ ድንገተኛ (Emergency) እና አስቀድሞ ቀጠሮ የተያዘላቸውን (Elective) ህክምናዎች ጨምሮ በአማካይ 550 ሰዎች የህክምና አገልግሎት ያገኛሉ።

​እንደ ዶ/ር ዳንኤል ማብራሪያ፣ በወር ውስጥ ከጠቅላላው የሥራ እንቅስቃሴ ውስጥ አንበሳውን ድርሻ የሚይዘው ቀጠሮ የተያዘላቸው (Elective) ቀዶ ጥገናዎች ሲሆኑ፣ በአማካይ 175 ያህሉ ደግሞ በድንገተኛ (Emergency) የቀዶ ጥገና ክፍል ውስጥ የሚስተናገዱ ናቸው።

ሆስፒታሉ የጀመረውን የስፔሻላይዜሽንና የሰብ-ስፔሻላይዜሽን ጉዞ በጠንካራ መሠረት ላይ ለመገንባት በከፍተኛ የሙያ ብቃት የተደራጁ የኮንሰልታንት (ከፍተኛ ስፔሻሊስት) ሐኪሞች ስምሪት ያደረገ ሲሆን፣ በዚህም መሠረት 12 የጠቅላላ ቀዶ ጥገና፣ 8 የላፓራስኮፒ፣ 6 የጆሮ፣ አፍንጫና ጉሮሮ (ENT)፣ 6 የአጥንትና መገጣጠሚያ (Orthopedic) እንዲሁም 5 የፕላስቲክ ሰርጀሪ ከፍተኛ ስፔሻሊስቶች በቋሚነት እያገለገሉ ይገኛሉ። በተጨማሪም የሕክምና አገልግሎቱን ይበልጥ ስኬታማ ለማድረግ የነርቭና ጭንቅላት (Neurosurgery)፣ የሽንትና ፍሳሽ ማውጫ ሥርዓት (Urology)፣ የሕፃናት (Paediatric) እና የልብና ደረት (Cardiothoracic) ቀዶ ጥገና ዘርፎች እያንዳንዳቸው በ3 ኮንሰልታንት ሐኪሞች የተደራጁ ሲሆን፣ የዕጢና ጡት (Endocrine and Breast) እንዲሁም የታችኛው የጨጓራና አንጀት (Lower GI) ሕክምናዎች ደግሞ እያንዳንዳቸው በ2 ከፍተኛ ስፔሻሊስቶች ይመራሉ። ተቋሙ በሰብ-ስፔሻላይዜሽን ዘርፍ ያለውን አቅም ይበልጥ በማሳደግ የደም ሥር (Vascular)፣ የጉበትና የሐሞት ከረጢት (Hepatobiliary) እና የላይኛው የጨጓራና አንጀት (Upper GI) ቀዶ ጥገናዎችን እያንዳንዳቸውን በአንድ አንድ ከፍተኛ የኮንሰልታንት ሐኪም በማዋቀር ለታካሚዎች ምሉዕና ተደራሽ የሆነ የሕክምና ዋስትና እየሰጠ ይገኛል።

በተጨማሪም 6 የላቁ የማደንዘዣ ስፔሻሊስቶች (Anesthesiologists)፣ 1 ልዩ የህፃናት ማደንዘዣ ስፔሻሊስት (Pediatric Anesthesiologist) እና 35 የኦፕሬሽን ክፍል አንስቴቲስቶች (Anesthetists) ተመድበዋል። 32 በሙያው ልዩ ክህሎት ያገበቱና የተካኑ ስፔሻላይዝድ የቀዶ ጥገና ክፍለ-ሥራ ነርሶች (OR Nurses) የሙያ አጋርነታቸውን እያበረከቱ ይገኛሉ።

​ሆስፒታሉ ካለው ሰፊ የክሊኒካዊ አገልግሎት እና የበለፀገ የሰብ-ስፔሻላይዜሽን ተሞክሮ አንጻር፣ የሀገሪቱ አንጋፋ የህክምና ተቋማት ዋነኛ የልምምድና የእውቀት መቅሰሚያ ማዕከል ለመሆን በቅቷል።

የጥቁር አንበሳ (አ.አ.ዩ) ተማሪዎች፦ በፕላስቲክ ሰርጀሪ (Plastic Surgery) እና በጆሮ፣ አፍንጫና ጉሮሮ (ENT) ህክምና ዘርፍ እውቀትና ትምህርታቸውን ለማጠናከርና ተግባራዊ ልምድ ለመቅሰም ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ይመጣሉ።

​የቅዱስ ጳውሎስ ተማሪዎች በተመሳሳይ መልኩ በራዲዮሎጂ (Radiology) ትምህርታቸው የላቀ ክሊኒካዊ ልምምድ ለማድረግ ከተቋሙ ጋር በትስስር (Affiliated) እየሰሩ ይገኛሉ።
​ዳይሬክተሩ ዶ/ር ዳንኤል አበበ ሆስፒታሉ እያሳየ ካለው አስደናቂ እድገትና የሰብ-ስፔሻላይዜሽን ስኬት ጎን ለጎን፣ በአንዳንድ የህክምና ዘርፎች ላይ የቁሳቁስና የመሣሪያ እጥረቶች ማጋጠማቸውን በግልጽ ጠቁመዋል።

​በተለይም በኦርቶፔዲክስ (Orthopedics) ዘርፍ በድንገተኛ የልዩ ልዩ የህክምና ዕቃዎች እጥረት ምክንያት በከፊል መስተጓጎል የሚታይ ሲሆን፤ በኒውሮ ሰርጀሪ (Neuro Surgery) ዘርፍ ደግሞ ለቀዶ ጥገና እጅግ ወሳኝና መነሻ የሆነው የሬዲዮግራፊክ ምስል ማሳያ መሣሪያ (C-arm) በአሁኑ ወቅት ባለመኖሩ ምክንያት ዘርፉ ሙሉ አቅሙን እንዳይጠቀም ማነቆ ሆኖበታል።

​ኮሌጁ እነዚህን የቁሳቁስና የዘመናዊ መሣሪያዎች እጥረቶች በዘላቂነት ለመቅረፍ እና ለአገልግሎቱ ምሉዕነት ከሚመለከታቸው የመንግሥትና አጋር አካላት ጋር በከፍተኛ ትኩረት እየሰራ መሆኑን ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።

ባለፉት ሁለት ዓመታት የተመዘገቡት ስኬቶች ግን ተቋሙን በሀገሪቱ የህክምና ታሪክ ውስጥ ተመራጭና ተወዳዳሪ የሰብ-ስፔሻላይዜሽን ማዕከል እያደረጉት እንደሚገኝ በልበ-ሙሉነት ገልጸዋል።

📍 የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን

📅 ግንቦት 26/2018 ዓ.ም
📍
📌 Follow Us on Social Media
👉 Facebook:
https://www.facebook.com/profile.php?id=100063650457050

👉 Telegram: Join Our Channel https://t.me/Y12HMCC

👉 Follow us on tiktok
https://vm.tiktok.com/ZMHWJyPGKQmQp-dftjE

🔖 💛✨

የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የዐይን ሕክምና ክፍል ቡድን በዛሬው ዕለት በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን መንከባከቢያ በጎ አድርጎት ማኅበር በመገኘት ለ300 ተረጂዎች ነፃ ...
27/05/2026

የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የዐይን ሕክምና ክፍል ቡድን በዛሬው ዕለት በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን መንከባከቢያ በጎ አድርጎት ማኅበር በመገኘት ለ300 ተረጂዎች ነፃ የዐይን ምርመራና የሕክምና አገልግሎት ሰጥቷል።

የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ
ግንቦት 19/2018 ዓ.ም

በበጎ ፈቃድና በሰብአዊ አገልግሎት መንፈስ የተከናወነው ይህ መርሐ ግብር አረጋውያንንና የአዕምሮ ሕሙማንን በአክብሮትና በፍቅር ለማገልገል ያለውን ቁርጠኝነት ያሳየ ሲሆን፣ ተገልጋዮቹም ለተደረገላቸው ድጋፍ ከፍተኛ ደስታና ምስጋና አቅርበዋል።

ለዚህ ድንቅና አስቀኚ ተግባር ለበጎ ዓላማው ላደረጉት ድጋፍ ባለሙያዎቹ፦ የሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁን አስተዳደርና ልማት ምክትል ፕሮቮስት አቶ ዓለሙ ክብረት፣ የንብረትና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ናትናኤል ታደሠን እና ሹፌር አቶ ተፈሪ ከልብ አመስግነዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ የተሳተፉት 9 የሚደርሱ የዐይን ሕክምና ባለሙያዎች “ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሚችለው መጠን ለወገኑ ሲደርስና ሲረዳ እኛም በዕውቀታችን ለበጎ ሥራ መሰለፍ አለብን” በማለት የማኅበራዊ ኃላፊነት መንፈስ መጠናከር እንዳለበት ገልጸዋል።

በተጨማሪም የመቄዶንያ ማኅበር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ ክቡር ዶ/ር ብንያም በለጠ፣ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ሁልጊዜ እየመጣ የሕክምና አገልግሎት ስለሚሰጠን በምንከባከባቸው አረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን ስም ከልብ እናመሰግናችኋለን ብለዋል።

በሌላ በኩል የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የዐይን ሕክምና ክፍል ከEyu Eye Center እና Cure Blindness Project ጋር በመተባበር ለ300 ሰዎች ነፃ የዐይን ሞራ (Cataract) ቀዶ ጥገና ለመስጠት ዝግጅቱን አጠናቋል።

በዚህ መሠረት የቅድመ ልየታ ምርመራው ከግንቦት 17 እስከ 29/2018 ዓ.ም የሚካሔዠድ ሲሆን፣ የቀዶ ጥገና ፕሮግራሙ ደግሞ ከሰኔ 11 እስከ 13/2018 ዓ.ም ይካሔዳል።

በመጨረሻም ይህ ዓይነቱ ሰብአዊ አገልግሎት በማኅበረሰቡ ውስጥ የመረዳዳትን፣ የፍቅርንና የአንድነትን ባህል ከፍ የሚያደርግ መሆኑ ተገልጿል።

“ሰውን ለመርዳት ሰው መሆን በቂ ነው!”

'To help a person, being human is enough!'

መልካም ቀን

📍 የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን

📅 ግንቦት 17/2018 ዓ.ም
📍
📌 Follow Us on Social Media
👉 Facebook:
https://www.facebook.com/profile.php?id=100063650457050

👉 Telegram: Join Our Channel https://t.me/Y12HMCC

👉 Follow us on tiktok
https://vm.tiktok.com/ZMHWJyPGKQmQp-dftjE

🔖 💛✨

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል አደረሰን፣ አደረሳችሁ!ስለዒድ አል-አድሐ “ዐረፋ” በዓል ስናስብ ሦስት ነገሮች ቀድመው ይታወሱናል። መስዕዋትነት፣ መታዘዝ እና መተጋገዝ። አባት ል...
27/05/2026

እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል አደረሰን፣ አደረሳችሁ!

ስለዒድ አል-አድሐ “ዐረፋ” በዓል ስናስብ ሦስት ነገሮች ቀድመው ይታወሱናል። መስዕዋትነት፣ መታዘዝ እና መተጋገዝ። አባት ልጁን ለመስዕዋት ያቀረበበት፤ ልጅ የአባቱን ትዕዛዝ የፈጸመበት፤ ሙስሊሞች የመተጋገዝን እሴት ለዓለም የገለጡበት በዓል ስለሆነ “ዐረፋ” በሕዝበ-ሙስሊሙ ዘንድ ትልቅ ትርጉም አለው።

እስማኤል ለነብዩ ኢብራሂም የመጀመሪያ እና ተወዳጅ ልጃቸው ነው። አላህ (ሱ.ወ.) ይሄን ተወዳጅና የመጀመሪያ ልጅ እንዲሠዉለት ሲጠይቃቸው ታዘዙ እንጂ ወደኋላ አላሉም። ለመታዘዝ የሞከሩት ነገሩ ቀላል ሆኖ አይደለም። ልጅን ያህል ነገር መስዕዋት ማድረግ ምኑ ይቀላል? የአባትነት ስሜት ይተናነቃል። የሰይጣን ሹክሹክታ ይፈታተናል። የቤተዘመድን ወቀሳ እና የጎረቤትን አስተያየት መቋቋምም ይከብዳል። ነብዩ ኢብራሒም፥ በዚህ ሁሉ አጣብቂኝ ውስጥ አንድ ሐቅ ተገልጦላቸዋል። ከራስ ስሜት፣ ከሰው ሐሜት እና ከወዳጅ ፍላጎት የሚልቅ ታላቅ ዓላማ እንዳለ አምነዋል። ስለዚህም በፈተና ውስጥ ጸንተው ቆሙ፤ ቆራጥነታቸውም በተግባር ታየ።

ሀገር የምትገነባው ከራስ ጥቅም በላይ በሚያስቡ እና ከግላዊ ፍላጎታቸው በላይ ለመፈጸም በቆረጡ ዜጎች ነው። የሚወዱትን ነገር እንኳን ሳይቀር ለመሠዋት ዝግጁ የሆኑ ዜጎች ሲበዙላት ሀገር ትበረታለች። እስማኤላቸውን ለመስጠት የማያመነቱ ዜጎች የሞሉባት ሀገር ጽኑ ናት።

የለመድናቸው፣ የምንወዳቸው፣ የራሳችን ገንዘብ ያደረግናቸው ብዙ ነገሮች ይኖራሉ። ከእነዚህ የሚበልጥ ዓላማ ግን አለ፤ እሱም “ሀገርነት እና ሉአላዊነት” ይሰኛል። ሀገርነት የሚገነባው ከመውሰድ ይልቅ በመስጠት ነው። ሉአላዊነት የሚጸናው በፈተና ሳይወድቁ በመቆም፤ በወጀብ ሳይናወጡ መጓዝ በመቻል ነው።

የእውነት ኢትዮጵያ ሲያልፍላት ማየት የምንሻ ከሆነ ምኞታችን በተግባር ይገለጥ። የሀገር ኩስመና ካሳሰበን ለግዝፈቷ እንድከም። ያጎበጣትን የድህነት ቋጥኝ ለመሸከም ትከሻችንን እናመቻች። ጎተራዋ እንዲሞላ እጃችን አፈር ይንካ። የጠየመ ገጽዋ እንዲፈካ በሥራ ሌት-ተቀን እንሰለፍ። የተቀማ ክብሯ እስኪመለስ ድርሻችንን እንወጣ። ሀገር መውደዳችን ከልብ ከሆነ መስዕዋት ለመሆን አናመንታ።

የዐረፋ በዓል የመታዘዝና የመስዕዋት ብቻ ሳይሆን የመደጋገፍና የመተጋገዝ በዓል ጭምር ነው። በዐረፋ ከሚከናወነው እርድ አንድ ሦስተኛው ለምስኪኖች እንዲሰጥ የእስልምና አስተምህሮ ያዛል። በዐረፋ ሕዝበ-ሙስሊሙ ደስታና ሐዘኑን እየተጋራ በዓሉን ያከብራል። የዐረፋ እለት አንድም ሰው ተከፍቶ አያሳልፍም፤ በዐረፋ ሰሞን ማንም ሰው ተርቦና ተጠምቶ አያድርም። በዓሉ ትርጉም የሚሰጠው ሕዝበ-ሙስሊሙ ያለውን ተካፍሎ ሲያከብረው ነው። ሰዎች አስቸጋሪ ሁኔታን የሚሻገሩበት መፍትሄው መተሳሰብና መተጋገዝ እንደሆነ ከዐረፋ እንማራለን። ሀገርም ከፈተናዎችዋ በላይ እንድትሆን እኒህ እሴቶች ወሳኝ ናቸው።

ዐረፋ ማኅበረሰባዊ በዓል የሚባለው ለዚህ ነው። ሰዎች በግላቸው የሚያከብሩት አይደለም። ቤተሰቡ፣ ጎረቤቱ፣ ሠፈሩ፣ ከተማው የሚያከብረው በዓል ነው። ያላቸውና የሌላቸው፤ የሚችሉና የማይችሉ፤ ታላላቆችና ታናናሾች፤ ባለ ሥልጣናትና ተራ ዜጎች፣ በአንድነት የሚያከብሩት በዓል ነው። ሰው የሚኖረው በቤቱ ውስጥ አይደለም። በማኅበረሰቡ ውስጥ ነው።

ማኅበረሰባዊ ትሥሥርና ትብብር ለዜጎች እና ለሀገር ደኅንነት ወሳኝ ናቸው። ማኅበረሰባዊ ትሥሥር ስለሌሎች እንድናስብ፣ ስለሌሎች እንድንሠራ እና ስለ ሌሎች ዋጋ እንድንከፍል ያደርገናል። ራሳችንን በሌሎች ጫማ ላይ አቁመን እንድናይ ያስችለናል። የሁላችንም ሰላም፣ የሁላችንም ደኅንነት እና የሁላችንም ጥቅም ካልተከበረ በቀር የግላችንን ብቻ ልናስከብር እንደማንችል ያስገነዝበናል። ስለዚህም ማኅበራዊ ግዴታን እንደ ዜግነት ግዴታ ወስደን እንድንሠራ ያደርገናል።

ምርጫ ማኅበራዊና ዜግነታዊ ግዴታዎችን ከምንወጣባቸው የዴሞክራሲ መገንቢያ መሳሪያዎች መካከል ዋነኛው ነው። ያለ ሕዝብ ተሳትፎ ዴሞክራሲ አይሳካም። ያለ ምርጫም የሕዝብ ተሳትፎ ምሉዕ አይሆንም። የዴሞክራሲያችን መሰረት ጥንካሬው የሚለካው በተሳትፎአችን መጠን ነው።

የዘንድሮ ሀገራዊ ምርጫ ሀገረ-መንግሥታዊ ሥርዓታችን የሚጠነክርበት መሰረት ነው። የዴሞክራሲ ልምምዳችን አንድ ደረጃ ከፍ የሚልበት፤ የቀጣይ ዓመታት የሀገራችንን እጣ-ፈንታ የምንበይንበት፤ ከምንም በላይ ብዝሃ-ድምጽ የሚሰማበት የሕግ መወሰኛ ምክርቤት የምንመሰርትበት ወሳኝ አጋጣሚ ነው። በመሆኑም በዓሉን ስናከብር ዜግነታዊ ግዴታችንን ለመወጣት ብቻ ሳይሆን በካርዳችን ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለማረጋገጥ እየተዘጋጀን እንዲሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ።

በድጋሚ መልካም የዐረፋ በዓል እንዲሆን እመኛለሁ!
ዒድ ሙባረክ!!

ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ!
ግንቦት 18፣ 2018 ዓ.ም

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

Yekatit 12 HMC CPD Center Hosts International Clinical TrainingA professional clinical skills training titled “Point-of-...
26/05/2026

Yekatit 12 HMC CPD Center Hosts International Clinical Training

A professional clinical skills training titled “Point-of-Care Ultrasound and Regional Anesthesia Skills to Improve Peri-Operative Safety and Patient Care” has been successfully conducted at the Continuing Professional Development (CPD) Center of Yekatit 12 Hospital Medical College under the organization of the Ethiopian Society of Anesthesiology Critical Care and Pain Medicine Physicians.

The training focused on strengthening patient safety during peri-operative care, enhancing the quality of healthcare service delivery, and improving practical competencies in Point-of-Care Ultrasound and Regional Anesthesia. Participants received intensive hands-on clinical training designed to advance practical medical skills and evidence-based clinical practice.

The first round of the training was conducted from May 18 to May 21, 2026, and concluded successfully. The second round, which commenced on May 25, 2026, is currently underway and will continue through May 28, 2026, at the CPD Center of Yekatit 12 Hospital Medical College.

During the closingof the 1st session, the Ethiopian Society of Anesthesiology Critical Care and Pain Medicine Physicians expressed its appreciation to the CPD Center of Yekatit 12 Hospital Medical College, recognizing the center as an ideal and professionally organized environment for hands-on clinical training.

The society further commended the CPD coordination team for its professionalism, positive engagement, and continued commitment to advancing professional medical education.

According to Mr. Guchi Tamru, CPD Coordinator at Yekatit 12 Hospital Medical College, the institution remains committed to strengthening the practical competencies of healthcare professionals and expanding high quality continuing professional development programs aimed at improving healthcare standards and patient outcomes.

📍 Yekatit 12 Hospital Medical College

📅 May 26, 2026
📍
📌 Follow Us on Social Media
👉 Facebook:
https://www.facebook.com/profile.php?id=100063650457050

👉 Telegram: Join Our Channel https://t.me/Y12HMCC

👉 Follow us on tiktok
https://vm.tiktok.com/ZMHWJyPGKQmQp-dftjE

🔖 💛✨

የግል ህክምና በተቋማችን በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ  በግል ህክምና በኘላስቲክና ሪኮንስትራክቲቭ ቀዶ ህክምና የምንስጣቸው የህክምና አገልግሎቶችየተለያየ የሰዉነት ክፍል ጠባሳዎችን ...
26/05/2026

የግል ህክምና

በተቋማችን በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በግል ህክምና በኘላስቲክና ሪኮንስትራክቲቭ ቀዶ ህክምና የምንስጣቸው የህክምና አገልግሎቶች

የተለያየ የሰዉነት ክፍል ጠባሳዎችን ማጥፋት

የሰዉነት ላይ እባጭና ካንሰር በፕላስቲክ ቀዶ ሕክምና ማስወገድ

የቆዳ ካንሰር ቀዶ ህክምና

የጡት ማሣነሥ ቀዶ ህክምና

የወንድ ልጅ ጡት እብጠት ማስወገድ

የነርቭ ቀዶ ህክምና

የእጅ ቀዶ ህክምና

የፊት: አፍንጫ: ጆሮ እና ከንፈር አደጋዎችን ማከም
በቃጠሎ የተጨማደደ አካላትን ማላቀቅ

ውስብስብ የእጅ አጥንት ስብራት: የእጅ መደንዘዝ ፡

የነርቭ እና የጅማት እንዲሁም በተፈጥሮ የእጅ መጣበቅ እና ትርፍ ጣት ቀዶ ሕክምና

አልድን ያለ ቁሰል ቆዳ በማልበስ በ skin graft ማከም

እነዚህንና ሌሎች ተጭማሪ የፕላስቲክ ቀዶ ሕክምና አገልግሎቶችን በተቋማችን ያገኛሉ

22/05/2026

የጥገና ሥራ ለማከናወን የሚቋረጥ የኃይል አቅርቦት

ነገ ግንቦት 15 ቀን 2018 ዓ.ም የጥገና ሥራ ለማከናወን በአዲስ አበባ፣ ሸገር፣ ነቀምትና ወልድያ ከተሞች የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥባቸው ቦታዎች ፦

✅ ከጠዋቱ 2:00-9:30

👉 ቡራዩ ድሬ ከአስፋልትበላይ፣ ገፈርሳ ውሀ ግድብ እና አካባቢው፣ ሲሊ፣ ከረላ፣ መናገሻ፣ ግብፅ ኤምባሲ፣ 6 ኪሎ ዩኒቨርስቲ፣ የካቲት 12 ሆስፒታል፣ ኤፍቢ ግቢ፣ ናይጄሪያ ኤምባሲ፣ 20 ቀበሌ፣ አምባሳደር አካባቢ፣ ሸራተን ፣ የውጭ ጉዳይ ፣ ታችኛው ቤ/መንግስት፣ ባሻወልዴ ኮንዶሚኒየም ፣ ቱሪስት ጀርባ ኮንዶሚኒየም

✅ከጠዋቱ 3:00-12:00

👉 አሻዋ ሜዳ ታጠቅ ሙገር ሲሚንት ፋብሪካ፣ ጂፕሰም ፋብሪካ፣ ጣፎ፣ MNS ሚሽን፣ 44 ማዞሪ እና አካባቢው የኃይል አቅርቦት ተቋርጦ ይቆያል፡፡

✅ ከጠዋቱ 2:00-10:30

👉በነቀምቴ ሪጅን ደምቢደሎ ከተማ፣ ደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲ፣ ደምቢዶሎ አየር ማረፊያ፣ ሙጊ ከተማ፣ ረቡዕ ገበያ፣ መቻራ እና በአካባቢው (ግንቦት 15-17/2018 ዓ/ም)

✅ ከጠዋቱ 2:00-6:30

👉 በወልድያ ሪጅን መቻሬ፣ አዳጎ፣ ሰዋሜዳ፣ አመያመጫ፣ ሁርጌሳ፣ ኡድመን፣ ልብሶ፣ ጊረና፣ መሀለምብ

ስለሆነም በአካባቢው የምትገኙ ክቡራን ደንበኞቻች የጥገና ሥራው ተጠናቆ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትእግስት እንድትጠብቁን በአክብሮት እናሳስባለን፡፡

EthiopianElectricUtility

🏥 በየካቲት ከአደጋ ወደ ተስፋ እና አዲስ ሕይወት!​በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ስር የሚገኘው የቃጠሎ ሕክምና የምርጥነት ማዕከል (Center of Excellence)፣ ከመላው ኢትዮ...
21/05/2026

🏥 በየካቲት ከአደጋ ወደ ተስፋ እና አዲስ ሕይወት!

​በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ስር የሚገኘው የቃጠሎ ሕክምና የምርጥነት ማዕከል (Center of Excellence)፣ ከመላው ኢትዮጵያ አቅጣጫዎች በከፍተኛ ስቃይና ጭንቀት ውስጥ ሆነው ለሚመጡ ታካሚዎች ዘመናዊ፣ የተቀናጀና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የሕክምና አገልግሎት በመስጠት እውነተኛ የሕይወት ታዳጊና የተስፋ ብርሃን እየሆነ ይገኛል።

​የቃጠሎ አደጋ በሰውነት ላይ ከሚያደርሰው አካላዊ ጉዳት ባሻገር፣ በታካሚው ስነ-ልቦና፣ ማህበራዊ ሕይወትና የኢኮኖሚ አቅም ላይ የሚያሳድረው ተጽዕኖ እጅግ የጎላ ነው። ይህንን እውነታ በሚገባ የሚረዳው ማዕከላችን፣ የሕክምና ሳይንስን ከልባዊ ሰብአዊ እንክብካቤ ጋር አዋህዶ በመተግበር ታካሚዎች በአማካይ ከ27 እስከ 38 ባሉት ቀናት ውስጥ በፍጥነት አገግመው ወደ ቀድሞ ማህበራዊ ሕይወታቸው እንዲመለሱ በትጋት እየሰራ ነው።

​ለዚህ ስኬታማ ጉዞ በስተጀርባ በዕውቀታቸውና በደግነታቸው የሚታወቁ ባለሙያዎች የተሳተፉበት ጠንካራ ቡድን አለ፦

​👨‍⚕️ 5 የፕላስቲክና ሪኮንስትራክቲቭ ሰርጀሪ ስፔሻሊስቶች (ከፍተኛ ቀዶ ሕክምና የሚያደርጉ)

​👩‍⚕️ 3 አጠቃላይ ሐኪሞች (ታካሚዎችን በቅርበት የሚከታተሉ)

​🩺 12 ልምድ ያላቸውና በዘርፉ የሰለጠኑ ነርሶች

​ይህ የሕክምና ስብስብ እንደ ስኳር፣ ደም ግፊት እና ኤች.አይ.ቪ ያሉ ተጓዳኝ የጤና እክሎች ያሉባቸውን ታካሚዎች ሳይቀር ልዩ ክትትል በማድረግ ሌት ተቀን በቅንጅት ያገለግላል።

​ማዕከሉ የታካሚዎችን ስቃይ ለመቀነስና የቆዳ ማገገምን ለማፋጠን ዘመናዊ የሕክምና መሠረተ ልማቶችን አሟልቷል፦

​💧 የሃይድሮ ቴራፒ (Hydrotherapy) ክፍል፦ ልዩ የውሃ ሕክምና በመስጠት ቁስልን ያጸዳል።

​🩹 ልዩ የቁስል አጠባና የኮፐር ክሬም አጠቃቀም፦ ኢንፌክሽንን በመከላከል ቁስሉ በፍጥነት እንዲድን ያደርጋል።

​🧬 የቆዳ ንቅለ ተከላ (Skin Grafting)፦ ታካሚዎች ሳይዘገዩ ለቆዳ ንቅለ ተከላ ብቁ እንዲሆኑ ይረዳል።

​🥗 የኒውትሪሽን ድጋፍ፦ በተለይ ለሕጻናት ታካሚዎች ፈጣን ማገገም በራሱ በሆስፒታሉ ተቀምሞ የሚዘጋጅ የተመጣጠነ ምግብ አቅርቦት ተዘርግቷል።

​የማዕከሉ ትልቁ መለያ ባህሪ ግን ሕክምናን በገንዘብ ብቻ አለመለካቱ ነው፤ በተለይም የአልጋ ክፍያ፣ የምግብ እና የመድኃኒት ወጪዎችን መሸፈን ለተሳናቸው አቅመ ደካማ ወገኖች ሙሉ ድጋፍ በማድረግ ሰብአዊ አገልግሎቱን አጠናክሮ ቀጥሏል።

​🤝 በዚህ ቅዱስ ተግባር ላይ ታማኙ "ማርናት ፋውንዴሽን" (Marnat Foundation) ከማዕከሉ ጋር በጽኑ በመተባበር፣ የአቅመ ደካሞችን ወጪ በመሸፈን የገንዘብና የቁሳቁስ ድጋፉን ያለሰልስ እያበረከተ ይገኛል።

​✨ የየካቲት 12 ሆስፒታል የቃጠሎ ሕክምና ማዕከል—በከፍተኛ የሕክምና ብቃት፣ በላቀ ሰብአዊነትና ፍጹም ተስፋ ላይ ተመስርቶ የብዙዎችን ሕይወትና መልክ የሚቀይር የፈውስ ማዕከል!

📍 የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን

📅 ግንቦት 13/2018 ዓ.ም
📍
📌 Follow Us on Social Media
👉 Facebook:
https://www.facebook.com/profile.php?id=100063650457050

👉 Telegram: Join Our Channel https://t.me/Y12HMCC

👉 Follow us on tiktok
https://vm.tiktok.com/ZMHWJyPGKQmQp-dftjE

🔖 💛✨

በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ነፃ የደም ግፊት እና የስኳር መጠን ምርመራ አገልግሎት እየተሰጠ ነው​የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ከአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በአይ...
21/05/2026

በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ነፃ የደም ግፊት እና የስኳር መጠን ምርመራ አገልግሎት እየተሰጠ ነው

​የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ከአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር በአይነቱ ልዩ የሆነ ነፃ የሕክምና ምርመራ አዘጋጅቷል። ይህ አገልግሎት የተዘጋጀው «ዓለም አቀፍ የደም ግፊት ቀን»ን (World Hypertension Day) በማስመልከት ሲሆን፣ ከግንቦት 9 እስከ ግንቦት 12 ቀን 2018 ዓ.ም. (እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ሜይ 17-20) ድረስ በተሳካ ሁኔታ እየተከናወነ ይገኛል።

​የዚህ መርሃ ግብር ዋና ዓላማ ማህበረሰቡ ስለ ደም ግፊትና ስኳር በሽታ ያለውን ግንዛቤ እንዲያሳድግ እና በጊዜ የመታየትና የመከላከያ ባህልን እንዲያዳብር ለማስቻል ነው።

​የምርመራው ዝርዝር መረጃዎች 📋

​የሚሰጡ አገልግሎቶች፦

🩸💉 ነፃ የደም ግፊት እና የስኳር መጠን ልኬት (Screening)

📅​ ከግንቦት 9 እስከ ግንቦት 12

🏢🌟​አጋር አካል፦ ከአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ጋር በጋራ የተዘጋጀ

👴👵👥​የታለመው የህብረተሰብ ክፍል፦ ሁሉም አዋቂዎች፣ በተለይም ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች

​የደም ግፊት እና የስኳር ህመም አብዛኛውን ጊዜ አስቀድሞ ምንም አይነት ግልጽ ምልክት ሳያሳዩ በሰውነታችን ውስጥ ሊሰወሩ የሚችሉ በመሆናቸው፣ አስቀድሞ መመርመርና ጤናን መከታተል ለነገ ህይወታችን ወሳኝ ነው።

​በመሆኑም የመርሃ ግብሩ አዘጋጆች ማናቸውም አዋቂ ሰው፣ በተለይም ደግሞ ዕድሜያቸው ከ40 ዓመት በላይ የሆኑ ዜጎች በሙሉ ወደ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በመምጣት ይህንን ነፃ የደም ግፊት እና የስኳር መጠን ልኬት አገልግሎት እንዲጠቀሙና ጤንነታቸውን እንዲያረጋግጡ ታላቅ ጥሪያቸውን ያስተላልፋሉ።

​«ጤናዎ በእጅዎ ነው፤ አስቀድመው በመመርመር ራስዎንና ቤተሰብዎን ከከፋ የጤና እክል ይከላከሉ!» 🍏🛡️

📍 የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን

📅 ግንቦት 13/2018 ዓ.ም
📍
📌 Follow Us on Social Media
👉 Facebook:
https://www.facebook.com/profile.php?id=100063650457050

👉 Telegram: Join Our Channel https://t.me/Y12HMCC

👉 Follow us on tiktok
https://vm.tiktok.com/ZMHWJyPGKQmQp-dftjE

🔖 💛✨

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yekatit 12 Hospital Medical College posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Yekatit 12 Hospital Medical College:

Share