Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS

Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS, 9. 046572, 38. 728670, Addis Ababa.

Ethiopian Pharmaceutical Supply service , EPSS
, procure ,manage and distribute RDF & Heath Programme Products for governmental health facilities to supply quality assured essential pharmaceutical with affordable prices & a sustainable manner in Eth

08/06/2026
አገልግሎት የ10 ወራት የሥራ አፈፃፀም ገመገመ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የ2018 ያለፉ አስር ወራት አጠቃላይ ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀም እንዲሁም ኢንሼቲቮች ታሳቢ ያደረገ የቀጣይ የሦሰት ወር ስራዎ...
03/06/2026

አገልግሎት የ10 ወራት የሥራ አፈፃፀም ገመገመ

፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የ2018 ያለፉ አስር ወራት አጠቃላይ ስራዎች ዕቅድ አፈፃፀም እንዲሁም ኢንሼቲቮች ታሳቢ ያደረገ የቀጣይ የሦሰት ወር ስራዎች ወይይት የአገልግሎቱ ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት ተገመገሞ አቅጣጫዎች አስቀምጠዋል

በቀረቡ ሀሳቦች ላይ ከሰራተኞች በተነሳ ጥያቄዎች ውይይት የተካሄደ ሲሆን ፤ የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር የቀጣይ የስራ አቅጣጫዎች አስቀምጠዋል ።

# ማገልገል ክብር ነው!
ማኅሌት አበራ

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ለተቋማችን የማህበራዊ ሚዲያ ተከታዮች፣ ለ...
27/05/2026

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ለተቋማችን የማህበራዊ ሚዲያ ተከታዮች፣ ለደንበኞቻችን እና ለመላው የሀገራችን ሙስሊም ማህበረሰብ በዓሉ የጤና፣ የሰላም፣ የፍቅር እና የደስታ እንዲሆንላችሁ ከልብ ይመኛል።

ይህ ታላቅ በዓል እርስ በእርስ በመረዳዳት፣ የታመሙትን በመጠየቅ እና የተቸገሩትን በመደገፍ በበጎነት የሚናፈቅበት እንዲሆን እንመኛለን።

ዒድ ሙባረክ!

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት

Hordoftoota amantaa Musliimaa hundaaf, baga ayyaana Iid Al-Adahaa (Arafaa) waggaa 1447ffaa nagaan geessan!

Tajaajilli Dhiyeessii Meeshaalee Maddaa Qorichaa Itoophiyaa, hordoftoota keenya marsariitiilee hawaasummaa, maamiltoota keenya fi guutuu ummata Musliimaatiif ayyaanni kun kan fayyaa, nageenyaa, jaalalaa fi gammachuu akka ta'u hawwii kootii gadi fagoo ibsa.

Ayyaanni guddaan kun wal-gargaaruun, kanneen dhukkubsatan gaafachuu fi hiyyeeyyii deeggaruun kan dabrurratti akka ta'u hawwina.

Iid Mubaarak!

Tajaajila Dhiyeessii Meeshaalee Maddaa Qorichaa Itoophiyaa

አገልግሎቱ ለተቸገሩ ወገኖች ማዕድ አጋራ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓልን ምክንያት በማድረግ ለተቸገሩ ወገኖች ማዕድ አጋርቷል...
27/05/2026

አገልግሎቱ ለተቸገሩ ወገኖች ማዕድ አጋራ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የኢድ አል አድሃ (አረፋ) በዓልን ምክንያት በማድረግ ለተቸገሩ ወገኖች ማዕድ አጋርቷል።

ድጋፍ የተከናወነው በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 05 በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ሲሆን ፤ ለተደረገው ማዕድ ማጋራት ምስጋና አቅርበዋል።

አገልግሎቱ ማህበራዊ ሀላፊነት የመወጣት ሂደት በቀጣይ አጥናክሮ ይቀጥላል።


ሰላም ይደግ

ዶ/ር አቡባካር ካምፖ የዩኒሴፍ ተወካይ በኢትዮጵያ አገልግሎቱን ጎበኙ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የዩኒሴፍ ተወካይ በኢትዮጵያ ዶ/ር አቡባካር ካምፖ(UNICEF- Ethiopia Country Dire...
21/05/2026

ዶ/ር አቡባካር ካምፖ የዩኒሴፍ ተወካይ በኢትዮጵያ አገልግሎቱን ጎበኙ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የዩኒሴፍ ተወካይ በኢትዮጵያ ዶ/ር አቡባካር ካምፖ(UNICEF- Ethiopia Country Director) እና ከፍተኛ አመራሮች አገልግሎቱን የጎበኙ ሲሆን፤ በአቅርቦት ሰንሰለቱ ላይ ባዩት ለውጦች ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል።

ዶ/ር አቡባካር ካምፖ እንዳሉት፤ የክትባት አያያዝ እና እስከ መጨረሻው ተጠቃሚ ድረስ የሚደረገው ስርጭት እጅግ አድናቆት የሚገባው መሆኑን ተናግረዋል።

በተጨማሪም የሀገር ውስጥ አምራቾችን ለማገዝ የተሰሩ ስራዎች የሚበረታቱ መሆናቸውን ጠቅሰው፣ በቀጣይም ኢትዮጵያ በሀገር ውስጥ የሕክምና ግብዓት የማምረት አቅሟን ይበልጥ ለማሳደግ ጠንክራ መስራት እንደሚገባት አሳስበዋል።

የአቅርቦት ሰንሰለት መሠረተ ልማት፣ የጤና የሰው ኃይል አቅም፣ የሕክምና ግብዓት አቅርቦት፣ እስከ መጨረሻው ተጠቃሚ ድረስ ለማድረስ የሚውሉ ተሽከርካሪዎች ድጋፍ፣ የክትባት ደህንነት እና አቅም ማሳደግ እንዲሁም የመረጃ ወቅታዊነትና ትክክለኛነትን ማሳደግ አገልግሎቱ ከዩኒሴፍ ጋር በጋራ ከሰራቸው በዋነኝነት የሚጠቀሱ መሆናቸውን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ አስረድተዋል።

እነዚህም ተግባራት የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር ትልቅ አስተዋፅኦ ማድረጋቸውን ገልፀዋል።

በቀጣይም በጋራ በሚሰሩባቸውና ድጋፍ በሚሹ ጉዳዮች ዙሪያ የተወያዩ ሲሆን፤ በዋናው ግቢ የሚገኙ መጋዘኖችንም ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

!
ማኅሌት አበራ

ከ180 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸዉ ኒዉሮሰርጂካል ማይክሮስኮፖች ድጋፍ ተደረገ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ሪች አናዘር ፋዉንዴሽን የተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ለጭንቅላት እና ህ...
19/05/2026

ከ180 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸዉ ኒዉሮሰርጂካል ማይክሮስኮፖች ድጋፍ ተደረገ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

ሪች አናዘር ፋዉንዴሽን የተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ለጭንቅላት እና ህብረሰረሰር ቀዶ ጥገና አገልግሎት የሚዉሉ ከ180 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገባቸዉ 3 ኒዉሮሰርጅካል ማይክሮስኮፖች የጤና ሚንስቴር ድኤታ ወ/ሮ ፍሬህይወት አበበ በተገኙበት ድጋፍ አድርጓል፡፡

ድጋፍ የተደረጉ መሳሪያዎች የማህበረሰቡን የጤና ተደራሸነት ለማጎልበት እና በዘርፉ ህክምናን ለማስተማር የሚረዳ ነዉ ሲሉ ወ/ሮ ፍሬህይወት ተናግረዉ ፤ ማይክሮስኮፖቹ ለባህርዳር ፣ ጎንደር እና ሀረመያ ዩንቨርሲቲ ሆስፒታሎች ተደራሽ እንደሚደረጉ ጠቁመዋል፡፡

ባለፈዉ በጀት አመት 5 ኒዉሮሰርጂካል ማይክሮስኮፖችን ድጋፍ እንዳደረጉ የሪች አናዘር ፋዉንዴሽን አስተባባሪ ዶ/ር ያዕቆብ ሰመረ አስታዉሰዉ መሳሪያዎቹ ከ2000 በላይ ታካሚዎች ከሀገር ዉጭ ይታከሙ የነበሩትን በሀገር ዉስጥ አገልግሎት እንዲያገኙ አስችሏል ብለዋል፡፡

አገልግሎቱ መሳሪያዎችን የተመረጡ ቦታዎች ላይ በአግባቡ የማድረስ እንዲሁም አስፈላጊዉን ክትትል እና ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆኑን የአገልግሎቱ ም/ዋና ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ንጉሴ ተናግረዉ ፤ ድጋፍ ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል፡፡

#ማገልገል ክብር ነዉ
ሰላም ይደግ

ጠንካራ አመራር ለህክምና ግብዓት አቅርቦት ስርዓት መዘመን ወሳኝ ነዉ፨፨፨፨፨፨፨፨፨አገልግሎቱ የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር ከአሜሪካ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ በማኔጅመንት ሳይንስ ፎር ሔል...
18/05/2026

ጠንካራ አመራር ለህክምና ግብዓት አቅርቦት ስርዓት መዘመን ወሳኝ ነዉ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨
አገልግሎቱ የአቅርቦት ሰንሰለቱን ለማጠናከር ከአሜሪካ መንግስት የገንዘብ ድጋፍ በማኔጅመንት ሳይንስ ፎር ሔልዝ የአቅርቦት ሰንሰለት ማጠናከሪያ ፕሮጀክት (United States Government funded Supply Chain Strengthening Project (SCS) ) ጋር በመተባበር ከግንቦት 6 እስከ 9 2018 ዓ.ም ድረስ በአዳማ ከተማ ለአገልግሎቱ ከፍተኛ አመራሮች የግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ የተዘጋጀ ሲሆን ፤ አመራሩ ጠንካራ ፣ በጤና አቅርቦት ስርዓት ውስጥ ግልፅ እቅድ ያለዉ ፣ ተጠያቂ የሆነ ፣ ቅንጅታዊ አሰራርን ያጎለበተና ቀልጣፋ የውሳኔ ስርዓትን ያረጋገጠ እንዲሆን የሚያስችል ስልጠና ተሰቷል።

“እምነት ሁሉን የሚለውጥ ቁልፍ ነገር ነው።” ያሉት የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አብዱልቃድር ገልገሎ ፤ የአቅርቦት ስርዓቱ እንዲሳለጥ እዉነተኛ የተግባቦት ልምምድ ሊኖር ይገባል ብለዋል። ይህም ሊሰፍን የሚችለው እንዲህ ባለ ወቅታዊና በተግባር የተደገፈ የአመራር ስልጠና እንደሆነም ገልፀዋል።

በተጨማሪም ዋና ዳይሬክተሩ እንዳሉት የአቅርቦት ሰንሰለት ስርዓት በቁርጠኛ አመራር ተደግፎ የተጠያቂነትና የግልፀኝነት ስርዓትን ማረጋገጥ መቻል እንደሚገባ አስረድተዋል።

አሰልጣኝ ሙሉጌታ አባተ እንዳሉት በሳይንሳዊ መንገድ የአመራሩን ክህሎት በማሳደግ ጥሩ የአቅርቦት ሰንሰለት እንዲኖር የሚያስችል የምክክር ጊዜ እንደነበረ ጠቁመዉ የመድኃኒት እጥረትን ለመቀነስ፣ የአቅርቦት መቋረጥን ለመከላከልና የጤና አገልግሎት ተደራሽነትን ለማሻሻል ከፍተኛ ሚና አለው ብለዋል።

የአገልግሎቱ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠናዉ በጤና አቅርቦት ሰንሰለት (Health Supply Chain) ውስጥ ጠንካራ “አመራርና አስተዳደር” ለመድኃኒቶች፣ ክትባቶች፣ የላብራቶሪ ግብዓቶችና ሌሎች የሕክምና ቁሳቁሶች በትክክል እንዲገዙ፣ እንዲከማቹ፣ እንዲሰራጩ እና ለተጠቃሚዎች በጊዜው እንዲደርሱ ፣ ፖሊሲዎችና የአስተዳደር ሂደቶች በአግባቡ እንዲተገበሩ ወሳኝ ነዉ ብለዋል።

ስልጠናው በዙር የሚቀጥል ሲሆን የመጀመሪያውን ዙር በስኬት ላጠናቀቁ የስራ መሪዎች ከዋና ዳይሬክተሩ እጅ የምስክር ወረቀት አግኝተዋል ።

#ማገልገል ክብር ነዉ
አማኑኤል ወርቃየሁ

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሽሬ ቅርንጫፍ ሠራተኛን ማዕከል ያደረገ የሕፃናት ማቆያ አስመረቀ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሽሬ ቅርንጫፍ፣ የ...
12/05/2026

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሽሬ ቅርንጫፍ ሠራተኛን ማዕከል ያደረገ የሕፃናት ማቆያ አስመረቀ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሽሬ ቅርንጫፍ፣ የሠራተኞችን የሥራ ጫና በማቃለል ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ያስገነባውን የሕፃናት የቀን ማቆያ ክፍል በይፋ ሠሞኑን ማስመረቁን የአገልግሎቱ ሽሬ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ ሙልየ አብርሃ ተናገሩ።

የማቆያው ዋና ዋና ጥቅሞች

✅እናቶች ልጆቻቸው በአቅራቢያቸውና አስተማማኝ ቦታ መሆናቸውን በመተማመን ሙሉ ትኩረታቸውን ለሥራቸው እንዲሰጡ ያስችላል።

✅ በሠራተኞች ላይ ሊፈጠር የሚችለውን የስነ-ልቦና ጫና በመቀነስ የሥራ ተነሳሽነትን ከፍ ያደርጋል።

✅ ሰራተኞች በስራቸው ላይ እንዲያተኩሩ በማድረግ የቅርንጫፉን የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት እና ፍጥነት ያሻሽላል።

በምረቃው ስነ-ስርዓት ላይ የተገኙት የሴቶች፣ ሕፃናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ሮ አለምጸሐይ ዳታ፤ የሕፃናት ማቆያው መገንባት ሴቶችን ከማብቃት እና የሥርዓተ-ፆታ እኩልነትን ከማረጋገጥ ባሻገር የሕፃናት ደህንነትና መብቶች ተጠብቀው እንዲያድጉ የላቀ አስተዋጽኦ እንዳለው ተናግረዋል።

በመርሃ-ግብሩ ላይ የሰሜን ምዕራብ ዞን አስተዳደር፣ የሽሬ ከተማ ከንቲባ፣ የመዘጋጃ ቤት እና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊዎች፣ የከተማው አፈ-ጉባኤ፣ የምክር ቤት ተወካዮች እንዲሁም የሀገር ሽማግሌዎች ተገኝተዋል።

ማገልገል ክብር ነው!

የሀዘን መግለጫ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨በኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (ኢመአአ) የድሬዳዋ ቅርንጫፍ የስራ ባልደረባችን የነበሩት አቶ ጌታቸው ከበደ ወልደዮሀንስ ባደረባቸው ህመም በህክምና ...
12/05/2026

የሀዘን መግለጫ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (ኢመአአ) የድሬዳዋ ቅርንጫፍ የስራ ባልደረባችን የነበሩት አቶ ጌታቸው ከበደ ወልደዮሀንስ ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው፣ በ58 ዓመታቸው ግንቦት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ላይ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

አቶ ጌታቸው በድሬዳዋ ቅርንጫፍ በሹፌርነት በሰሩባቸው ዓመታት ሁሉ ሙያቸውን በቅንነትና በትጋት ያገለገሉ፣ "ደከመኝ ሰለቸኝ" የማያውቁ ብቁ ሰራተኛ ነበሩ።

ላሳዩት የላቀ የስራ አፈጻጸምም በተለያዩ ጊዜያት የዕውቅና ተሸላሚ መሆናቸው ይታወሳል። በግል ህይወታቸውም ባለትዳርና የሁለት ሴት እንዲሁም የሁለት ወንድ ልጆች አባት ነበሩ።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት በአቶ ጌታቸው ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና ለሥራ ጓደኞቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ ከ9.4 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባቸውን የህፃናት ማቆያ ማዕከል እና የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት መርቆ አገ...
11/05/2026

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጎንደር ቅርንጫፍ ከ9.4 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያስገነባቸውን የህፃናት ማቆያ ማዕከል እና የንፁህ መጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በዛሬው ዕለት መርቆ አገልግሎት ላይ አዋለ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በምረቃ ስነ-ሥርዓቱ ላይ የተገኙት የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አወቀ አስፈሬ እንደገለጹት፤ ተቋሙ የአገልግሎት አሰጣጡን በዲጂታል ቴክኖሎጂ ከማዘመን ባለፈ፣ የሰራተኞቹንና የህዝብን የመልካም አስተዳደር ችግሮች ለመቅረፍ እያከናወነ ያለው ተግባር አርአያነት ያለው ነው። አዲሱ የህፃናት ማቆያ ማዕከል በተለይም ለሰራተኛ እናቶች ምቹ የስራ አካባቢን እንደሚፈጥርና የተቋሙን የውሃ ችግር በዘላቂነት እንደሚቀርፍም አክለዋል።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ አካቶ ትግበራ ዳይሬክተር ወ/ሮ አለምፀሀይ ዳታ በበኩላቸው፤ ተቋሙ ለህፃናትና ለሴቶች ልዩ ትኩረት በመስጠት መሰል ግንባታዎችን እያከናወነ መሆኑን ገልጸዋል። እንደ ሀገር 19 ቅርንጫፎች ያሉት ይህ ተቋም፤ እንደ ወባ፣ ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ እና ቲቢ ያሉ መድኃኒቶችን ለጤና ተቋማት በነፃ እያከፋፈለ ይገኛል።

ወ/ሮ አለምፀሀይ አክለውም፣ የመድኃኒት አቅርቦቱን 100 በመቶ ለማድረስ ጥረት እየተደረገ መሆኑንና የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎችም ጭምር በቻርተር አውሮፕላን በመታገዝ የህክምና ግብዓቶችን ተደራሽ እያደረጉ መሆኑን አስታውቀዋል።

የጎንደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይሔይስ ስብሐት እንደተናገሩት፤ ቀደም ሲል የነበረው የህፃናት ማቆያ ለህፃናት ምቾት የማይሰጥ በቆርቆሮ የተገነባ ነበር። አሁን የተገነባው ዘመናዊ ማዕከል ግን አጥቢ እናቶች ስራቸውን በተረጋጋ ሁኔታ እንዲያከናውኑ ትልቅ ፋይዳ አለው። በተጨማሪም የተቋሙን የውሃ ጥም ለመቅረፍ የከርሰ ምድር ውሃ ልማት መከናወኑን ገልጸዋል።

ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቱ በአሁኑ ወቅት ለ6 ዞኖች አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን፤ በእጁም ከ837 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የህይወት አድን መድኃኒቶች ክምችት እንዳለውና ስርጭቱም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል በመድረኩ ተገልጿል።

Address

9. 046572, 38. 728670
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS:

Share