Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS

Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS, 9. 046572, 38. 728670, Addis Ababa.

Ethiopian Pharmaceutical Supply service , EPSS
, procure ,manage and distribute RDF & Heath Programme Products for governmental health facilities to supply quality assured essential pharmaceutical with affordable prices & a sustainable manner in Eth

ባህር ዳር ቅርንጫፍ ዓመታዊ የሕክምና ግብዓቶች ቆጠራን አጠናቆ ወደ መደበኛ ሥራ ለመመለስ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታወቀ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎትየኢትዮ...
13/07/2026

ባህር ዳር ቅርንጫፍ ዓመታዊ የሕክምና ግብዓቶች ቆጠራን አጠናቆ ወደ መደበኛ ሥራ ለመመለስ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታወቀ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎትየኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ባህር ዳር ቅርንጫፍ የ2018 ዓ.ም. ዓመታዊ የሕክምና ግብዓቶች ቆጠራን በተሳካ ሁኔታ በማጠናቀቅ ወደ መደበኛ የሥራ እንቅስቃሴው ለመመለስ ዝግጅቱን አጠናቋል።

የቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ አቶ አምሳሉ ጫኔ እንደገለጹት፣ የመጋዘን፣ የፋይናንስና ሌሎች አግባብነት ያላቸው የሥራ ክፍሎች በቅንጅትና በከፍተኛ ኃላፊነት በመሳተፋቸው የቆጠራው ሂደት ያለምንም መስተጓጎል ተጠናቋል ብለዋል።

አቶ አምሳሉ አክለውም፣ ከቆጠራው በፊት በቂ ቅድመ ዝግጅት በመደረጉና ሁሉም ተንጠልጣይ ሰነዶች (Outstanding Documents) በወቅቱ በመጠናቀቃቸው የቆጠራው ሥራ በታቀደው ጊዜና በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቅ ችሏል ሲሉ ገልፀዋል።

በተጨማሪም፣ ባለፉት ተከታታይ ዓመታት በቅርንጫፉ የተከማቹ የሕክምና ግብዓቶች ላይ ምንም ዓይነት ብልጫም ሆነ ጉድለት አለመመዝገቡን ጠቅሰው፣ ይህንን ውጤት ለማስቀጠል በመጋዘን አያያዝ፣ በውስጣዊ ቁጥጥርና በንብረት ጥበቃ ላይ የበለጠ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሠራ ተናግረዋል።

በመጨረሻም የቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ፣ ለቆጠራው ስኬታማ መጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ሁሉም የቅርንጫፉ ሠራተኞች ምስጋናቸውን ገልጸው፣ ተቋሙ ቀልጣፋና ጥራት ያለው የሕክምና ግብዓት አቅርቦት ለማረጋገጥ በቀጣይነት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።

የኢመአአ ጅማ ቅርንጫፍ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የህክምና ግብዓት ቆጠራ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን አስታወቀ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (ኢመአአ) የጅማ ቅርን...
12/07/2026

የኢመአአ ጅማ ቅርንጫፍ የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የህክምና ግብዓት ቆጠራ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን አስታወቀ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (ኢመአአ) የጅማ ቅርንጫፍ የህክምና ግብዓቶች ዓመታዊ ቆጠራን በተሳካ ሁኔታ ማካሄዱን ገለጸ። የቆጠራ ሥራው የመድኃኒቶችንና የሌሎች የህክምና ግብዓቶችን ትክክለኛ መጠን፣ ጥራትና የክምችት ሁኔታ በማረጋገጥ የንብረት አስተዳደርን ለማጠናከርና የአቅርቦት ሥርዓቱን ውጤታማነት ለማሳደግ ያለመ ነው።

የቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ አቶ እስማኤል ሸህኢሳ እንደገለጹት፤ ቆጠራው በዕቅድ መሠረት በተቀናጀ መንገድ ተከናውኗል። የተገኘው ውጤትም የክምችት ትክክለኛነትን በማሻሻል፣ ለወደፊቱ ፈጣንና ቀልጣፋ የህክምና ግብዓት ስርጭት ለመዘርጋት ትልቅ አስተዋጽኦ ይኖረዋል።

ቅርንጫፉ ከጊዜ ወደ ጊዜ አሠራሮችን እያሻሻለ መምጣቱን የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፤ ከዚህ ቀደም በከፍተኛ መጠን ይስተዋል የነበረውን የመድኃኒትና የህክምና ግብዓቶች ብክነት በእጅጉ በመቀነስ፣ በበጀት ዓመቱ ወደ ዜሮ ማምጣት መቻሉን አረጋግጠዋል። ከዚህ ጋር ተያይዞም የቆጠራ ሥራውን በየዓመቱ በማከናወን፣ የመድኃኒትና የህክምና ግብዓት አስተዳደርን ግልጽ፣ ተጠያቂና ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት እየተሠራ መሆኑን አቶ እስማኤል አክለው ገልጸዋል።

የኢመአአ ጋምቤላ ቅርንጫፍ ዓመታዊ የመድኃኒትና ሕክምና ግብዓቶች ቆጠራን አጠናቀቀ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (ኢመአአ) ጋምቤላ ቅርንጫፍ ከሐምሌ 1 እስከ 3 ቀ...
12/07/2026

የኢመአአ ጋምቤላ ቅርንጫፍ ዓመታዊ የመድኃኒትና ሕክምና ግብዓቶች ቆጠራን አጠናቀቀ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት (ኢመአአ) ጋምቤላ ቅርንጫፍ ከሐምሌ 1 እስከ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ሲያካሂድ የነበረውን ዓመታዊ የመድኃኒትና ሕክምና ግብዓቶች ቆጠራ በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቁን አስታወቀ።

የቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ችንግ ራንግ እንደገለጹት፤ በሂደቱ የመድኃኒትና ሕክምና ግብዓቶች አካላዊ ቆጠራ፣ የመረጃዎችን ወደ ኤሌክትሮኒክ ሥርዓት የማስገባት እንዲሁም የጉድለትና ብልጫ ማስታረቅ ሥራዎች በታቀደላቸው የሦስት ቀናት የሥራ መርሃ ግብር ውስጥ በብቃት ተከናውነዋል።

በዚህ ዓመታዊ የቆጠራ ሥራ ላይ የስርጭት፣ የዕቅድ፣ የክትትልና ግምገማ፣ የአስተዳደር እንዲሁም የፋይናንስ ክፍሎች ሠራተኞች በጋራና በቅንጅት ተሳትፈዋል። ከዚህ በተጨማሪም ሂደቱ ሙሉ በሙሉ ግልጽነት ባለው መልኩና መመሪያዎችን ተከትሎ እንዲከናወን የውስጥ ኦዲት እና የሥነ-ምግባር ኃላፊዎች በገለልተኛ ታዛቢነት መሳተፋቸውን ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል።

የዘንድሮው የቆጠራ ሂደት ከመጀመሩ በፊት የማዕከሉ ሠራተኞች በሙሉ በመተባበር መጋዘኖችን በጋራ ያጸዱ ሲሆን፤ ይህም ከፍተኛ የሥራ መነሳሳት፣ የተደራጀና ደህንነቱ የተጠበቀ የሥራ አካባቢ እንዲፈጠር ማስቻሉ ተገልጿል።

ይህ የተከናወነው ስኬታማ የቆጠራ ሂደት የኢትዮጵያን የጤና ሥርዓት ለማጠናከር እንደ ቅርንጫፍ ያለውን ወሳኝ ሚና በግልጽ የሚያሳይ መሆኑን አቶ ችንግ ራንግ አክለው ገልጸዋል።

@

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ነቀምቴ ቅርንጫፍ ዓመታዊ የሕክምና ግብዓት ቆጠራውን በፍጥነትና በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቁን አስታወቀ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨በቆጠራው ሂደት ላይ የመጋዘን ...
11/07/2026

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ነቀምቴ ቅርንጫፍ ዓመታዊ የሕክምና ግብዓት ቆጠራውን በፍጥነትና በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቁን አስታወቀ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በቆጠራው ሂደት ላይ የመጋዘን ኃላፊዎች፣ የፋይናንስ ባለሙያዎች እና ጉዳዩ የሚመለከታቸው የሥራ ክፍሎች በቅንጅት የተሳተፉ ሲሆን፣ ይህም የቆጠራ ሥራው ያለምንም መስተጓጎል በስኬት እንዲከናወን ትልቅ አገዝ አድርጓል።

የቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ገመቹ ፍቅሩ እንደገለጹት፤ የዕለት ተዕለት የክፍት ሽያጭ (Open sale) እና የውጪ ጭነቶች (Outbound) እንቅስቃሴዎች በየቀኑ የቅርብ ክትትል ሲደረግባቸው ቆይተዋል።

በመሆኑም በመጨረሻው ሰዓት ላይ ምንም ዓይነት ያልተጠናቀቁ ጠንጠልጣይ ሰነዶች (Outstanding) ባለመኖራቸው እና አስቀድሞ በቂ ቅድመ-ዝግጅት በመደረጉ፣ ቆጠራውን በአንድ ቀን ውስጥ በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቅ ተችሏል።

ባለፉት ሦስት ተከታታይ ዓመታት በቅርንጫፉ ምንም ዓይነት የህክምና ግብአቶች ብልጫም ሆነ ጉድለት እንዳልተመዘገበ የገለጹት ሥራ አስኪያጁ፣ ይህንን መልካም ስኬት ለማስቀጠልም በመጋዘን አያያዝ እና ጥንቃቄ ላይ ይበልጥ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።

በመጨረሻም ለዚህ ውጤት መገኘት የቅርንጫፉ ሠራተኞች ላሳዩት ከፍተኛ ትጋትና ታታሪነት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የ2018 ዓ.ም. ዓመታዊ የንብረት ቆጠራ አከናወነ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት "ጥራት ከፍጥነት በፊት" በሚል...
10/07/2026

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የ2018 ዓ.ም. ዓመታዊ የንብረት ቆጠራ አከናወነ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት "ጥራት ከፍጥነት በፊት" በሚል መሪ ቃል የ2018 ዓ.ም. ዓመታዊ የንብረትና የሕክምና ቁሳቁስ ቆጠራ አካሄደ።

ቆጠራው በአገልግሎቱ ዋና መሥሪያ ቤት፣ በቅርንጫፍ መጋዘኖችና በተለያዩ የሥራ ክፍሎች በተቀናጀ መልኩ ተከናውኗል።

የዚህ ፊዚካል ኢንቬንቶሪ (ቆጠራ) ዋና ዓላማ የተቋሙን ንብረቶች በአካል በመቁጠር ከመዝገብ ጋር ማመሳከር ሲሆን፤ ይህም የመረጃ ትክክለኛነትን ለማረጋገጥ፣ የንብረት አስተዳደርን ለማጠናከር፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ለማስፈን እንዲሁም ለቀጣይ ውሳኔ አሰጣጥ የሚረዱ ትክክለኛ መረጃዎችን ለማግኘት ታስቦ የተከናወነ ነው።

በቆጠራው ወቅት የተመደቡት የቆጠራ ቡድኖች ሂደቱን በተዘጋጁ መመሪያዎችና የአሠራር ሥርዓቶች መሠረት በጥራትና በትክክለኛነት አከናውነዋል።

"ጥራት ከፍጥነት በፊት" የሚለው መሪ ቃልም ተቋሙ በሁሉም የሥራ ሂደቶች ፍጥነትን ከመምረጥ ይልቅ ለጥራትና ለተጠያቂነት የሚሰጠውን ቅድሚያ የሚያሳይ ሲሆን፣ ይህም የመድኃኒት እጥረት እንዳይከሰት አስቀድሞ ለመከላከል ከፍተኛ አስተዋፅኦ አለው።

የቆጠራውን ሂደትና አፈጻጸም በተመለከተ ከዋና መሥሪያ ቤትና ከቅርንጫፎች የተውጣጡ ከ50 በላይ ተሳታፊዎች በበይነ-መረብ (Zoom) የጋራ ግምገማ አድርገዋል።

በዚሁ መሠረት፣ የቆጠራውን ትክክለኛነት ለመጠበቅ ሲባል በዋና መሥሪያ ቤቱና በሁሉም 19 ቅርንጫፎች የ ERP_SAP ሲስተም የዝውውር (Transaction) ሥራ ለጊዜው እንዲቆም ተደርጎ ቆጠራው ተካሂዷል።

እስካሁንም በ46 መጋዘኖች ውስጥ የገቡ የመረጃ ምዝገባዎች (Total Entries) 70,536 ደርሰዋል።

በግምገማው መሠረት እንደ አዳማ፣ አሶሳ፣ ባህር ዳር፣ ሰመራ፣ ጅጅጋ እና ነቀምቴ ያሉ ቅርንጫፎች ቆጠራውን ሙሉ በሙሉ ያጠናቀቁ ሲሆን፣ የሂሳብ ማመጣጠን (Inventory Balance Reconciliation) ሥራቸውን በመሥራት የብልጫና ጉድለት (Shortage and Overage) መረጃዎችን እያሳወቁ ይገኛሉ።

አገልግሎቱ ዓመታዊ የሕክምና ቁሳቁስና መድኃኒት ቆጠራውን ሙሉ በሙሉ አጠናቆ ሰኞ ሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ለደንበኞቹ መደበኛ አገልግሎት መስጠት በይፋ እንደሚጀምር አስታውቋል።

የቀብሪደኃር ቅርንጫፍ የህክምና ግብዓት ቆጠራው ዉጤታማ መሆኑን አስታወቀ፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ  አገልግሎት የቀብሪደኃር ቅርንጫፍ የህክምና ግብዓቶችን አመታዊ ቆጠራ በተሳካ ...
10/07/2026

የቀብሪደኃር ቅርንጫፍ የህክምና ግብዓት ቆጠራው ዉጤታማ መሆኑን አስታወቀ
፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የቀብሪደኃር ቅርንጫፍ የህክምና ግብዓቶችን አመታዊ ቆጠራ በተሳካ ሁኔታ አካሂዷል።

የቆጠራ ሥራው የመድኃኒቶችንና የሌሎች የህክምና ግብዓቶችን ትክክለኛ መጠን፣ ጥራትና የክምችት ሁኔታ በማረጋገጥ የንብረት አስተዳደርን ለማጠናከርና የአቅርቦት ሥርዓቱን ውጤታማነት ለማሳደግ ያለመ ነው።

የቅርንጫፉ ስራ አስኪያድ አቶ አብዲዋሊ ሀሰን እንደገለጹት፣ ቆጠራው በዕቅድ መሠረት በተቀናጀ መንገድ የተከናወነ ሲሆን የተገኙ ውጤቶችም የክምችት ትክክለኛነትን በማሻሻል ለወደፊቱ ፈጣንና ቀልጣፋ የህክምና ግብዓት ስርጭት አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ገልፀዋል።

አገልግሎቱ በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ ቅርንጫፎቹ የንብረት ቆጠራን በየዓመቱ በማከናወን የመድኃኒትና የህክምና ግብዓት አስተዳደርን ግልጽ፣ ተጠያቂና ውጤታማ ለማድረግ በትኩረት እየሠራ ይገኛል።

#ማገልገል ክብር ነዉ

የአገልግሎቱ አዳማ ቅርንጫፍ አመታዊ የንብረት ቆጠራውን  አጠናቀቀ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የአገልግሎቱ አዳማ ቅርንጫፍ አመታዊ የመድኃኒትና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች የንብረት ቆጠ...
10/07/2026

የአገልግሎቱ አዳማ ቅርንጫፍ አመታዊ የንብረት ቆጠራውን አጠናቀቀ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨

የአገልግሎቱ አዳማ ቅርንጫፍ አመታዊ የመድኃኒትና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች የንብረት ቆጠራን ከታቀደለት የጊዜ ሰሌዳ ቀድሞ በአንድ ቀን በተሳካ ሁኔታ ማጠናቀቁ ተገለጸ።

የቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ አቶ አስረስ ተሾመ እንደገለጹት፣ ቆጠራው በቅርንጫፉ የጥራት አስተዳደርና ቁጥጥር ባለሙያዎች ትብብር የመድኃኒቶችን ጥራትና ሁኔታ በመፈተሽ ያለምንም ችግር ተጠናቋል ብለዋል።

በቆጠራው ሂደት የአገልግሎቱ የኦዲት ባለሙያዎች በታዛቢነት በመገኘት የሂደቱን አጠቃላይ አፈጻጸም መከታተላቸውን ገልፀዋል።

የመጋዘን አስተባባሪው አቶ ክብረት ወንድአፍራሽ በበኩላቸው፣ ጥራታቸውና ፈዋሽነታቸው የተረጋገጡ መድኃኒቶችና የህክምና መገልገያ መሳሪያዎች በትክክል ተቆጥረው ወደ ኢ.አር.ፒ (ERP) ሲስተም በመመዝገብ ለስርጭት ዝግጁ መደረጋቸውን ተናግረዋል።

በመጨረሻም የቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ በቆጠራው ሂደት ወቅት ለተደረገው ትብብርና ቆጠራው በጥራትና በፍጥነት እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱ የቆጣሪ ኮሚቴ አባላትና ለሁሉም ባለድርሻ አካላት ማመስገናቸውን አቶ አለምነህ ንጉሴ የላኩልን መረጃ ያመለክታል።

የአገልግሎቱ አዲስ አበባ ቁጥር 1 ቅርንጫፍ በጥራት ላይ ያተኮረ የሕክምና ግብአቶች ዓመታዊ ቆጠራ እያካሄደ መሆኑን ገለጸ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የ...
10/07/2026

የአገልግሎቱ አዲስ አበባ ቁጥር 1 ቅርንጫፍ በጥራት ላይ ያተኮረ የሕክምና ግብአቶች ዓመታዊ ቆጠራ እያካሄደ መሆኑን ገለጸ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት የ2018 በጀት ዓመት የሕክምና ግብአቶች ዓመታዊ ቆጠራን በማዕከላዊ መጋዘኖች እና በሁሉም ቅርንጫፎች ከሐምሌ 01 ቀን ጀምሮ እያከናወነ ይገኛል፡፡

በዚህም የአገልግሎቱ አዲስ አበባ ቁጥር 1 ቅርንጫፍ፣ ቆጠራውን ከፍጥነት በተጨማሪ በጥራት ላይ ልዩ ትኩረት በማድረግ እያከናወነ እንደሚገኝ የቅርንጫፉ ሥራ አስኪያጅ አቶ እንዳለው አስማማው ገልጸዋል፡፡

ሥራ አስኪያጁ አክለውም፣ ቀደም ሲል በየሩብ ዓመቱ ይካሄድ የነበረው የክምችት ቆጠራ ክፍተቶችን ቀድሞ ለመለየትና ለማረም በማስቻሉ፣ የዘንድሮውን ዓመታዊ ቆጠራ በተሻለ ጥራትና ፍጥነት ለማከናወን ትልቅ አቅም መፍጠሩን ጠቁመዋል።

በቆጠራ ሂደቱ ላይ የተሰማሩ ባለሙያዎች ከጠዋት እስከ ምሽት በከፍተኛ ትጋትና ተነሳሽነት እየሠሩ መሆናቸውን የገለጹት አቶ እንዳለው፤ ለቅርንጫፉ ከፕሮጀክት ቢሮ እና ከዋና መሥሪያ ቤት አስፈላጊው ድጋፍና ክትትል እየተደረገላቸው እንደሚገኝም ተናግረዋል፡፡

በተመሳሳይ የሳሪስ 3 መጋዘን ኃላፊ ወ/ሮ መቅደላዊት በበኩላቸው፣ የቆጠራ ሥራው በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝና በአስተማማኝ ሁኔታ በ3 ቀናት ውስጥ ለማጠናቀቅ አቅደው እየሰሩ መሆኑን አስታውቀዋል።

አገልግሎቱ የሚያከናውነው ይህ ዓመታዊ የቆጠራ ሥራ፤ የሕክምና ግብአቶችን ትክክለኛ መረጃ በማረጋገጥ፣ የክምችት አስተዳደር ሥርዓትን በማሻሻል እና የመድኃኒት አቅርቦት ቀጣይነትን በአስተማማኝ ሁኔታ ለማጠናከር ወሳኝ ሚና ይጫወታል፡፡


ሰላም ይደግ!

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጅማ ቅርንጫፍ የደንበኞች ቀንን በውይይት አከበረ።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጅማ ቅርንጫፍ ‘‘ከደንበኞች ...
09/07/2026

የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጅማ ቅርንጫፍ የደንበኞች ቀንን በውይይት አከበረ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የኢትዮጵያ መድኃኒት አቅራቢ አገልግሎት ጅማ ቅርንጫፍ ‘‘ከደንበኞች ጋር ወደ ተሻለ ነገ’’ በሚል መሪ ቃል የደንበኞች ቀንን አክብሯል።

በበዓሉ ላይ ቅርንጫፉ የህክምና ግብዓቶችን ከሚያሰራጭባቸው የተለያዩ የጤና ተቋማት የመጡ ተወካዮችና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የጅማ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ አቶ እስማኤል ሼ/ኢሳ እንደገለጹት፤ ዕለቱን ማክበር ያስፈለገው የአገልግሎት አሰጣጡን ወቅታዊ ደረጃ ለመገምገም እና በቀጣይ አቅርቦቱን በጋራ ማሻሻል በሚቻልባቸው መንገዶች ላይ ለመወያየት ነው።

ተቋሙ ከደንበኞች ጋር ያለውን ቅርበት በማሳደግ የህክምና ግብዓቶችን ተደራሽ ለማድረግ በርካታ ስራዎችን ማከናወኑንም ጠቁመዋል።

የጅማ ጤና ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ኃያት ሁሴን በበኩላቸው፣ አገልግሎቱ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ የህክምና ግብዓት አቅርቦት ስርዓቱን እያሻሻለ መምጣቱን አውስተዋል።

ያሉትን ተግዳሮቶችና በቀጣይ መስተካከል ያለባቸውን ጉዳዮች ከተገልጋዩ ጋር ለመወያየት እንዲህ ዓይነት መድረክ መዘጋጀቱ የሚያስመሰግንና ሊጠናከር የሚገባው ተግባር መሆኑንም ገልጸዋል።

በመድረኩ ላይ በቅርንጫፉ የማርኬቲንግ ቡድን መሪ ወ/ሮ ማህሌት ሰሙንጉስ አማካኝነት ተቋማዊ የስያሜና የአሰራር ለውጦች፣ የዲጂታላይዜሽን ስራዎች፣ የውል አቅርቦት ስርዓት አፈጻጸም እና የህክምና ግብዓቶች ስርጭት ምጣኔን የተመለከቱ ሪፖርቶች ቀርበዋል።

በተጨማሪም የማርኬቲንግ ኦፊሰሩ አቶ ፈዬራ አበራ የአገልግሎቱና የግል ተቋማት የዋጋ ትንተና፣ የኮንትራት ዋጋዎች፣ የወቅታዊ ገበያ አጭር ጊዜ ትንተና እና የታቀዱ የገበያ ጣልቃ ገብነቶችን በዝርዝር አብራርተዋል።

በፕሮግራሙ ማጠቃለያ ላይ ተሳታፊዎቹ ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በጋራ በመፍታት የጤና ስርዓቱን ይበልጥ ማጠናከር፣ ግልጽነትና ተጠያቂነት በሰፈነበት መልኩ ፍትሃዊ አገልግሎት መስጠት እንዲሁም የአገልግሎት ልህቀትን በማስመዝገብ የደንበኞችን እርካታ ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ጥልቅ ውይይት አድርገዋል።

!
ማኅሌት አበራ

የህክምና ግብአቶች አቅርቦት
07/07/2026

የህክምና ግብአቶች አቅርቦት

Address

9. 046572, 38. 728670
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Ethiopian Pharmaceuticals Supply Service - EPSS:

Shortcuts

Share