04/06/2026
የአላሙራ ሆስፒታልማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ደስ አለን አላችሁ! 🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆
******************************
የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የቀዶ ህክምና አገልግሎት ላለፈው አንድ አመት ሲሰጥ የቆየ ቢሆንም አንድ ብቻ የቀዶ ህክምና አልጋ በመኖሩ በተፈጠረ የአቅም ውስንንት የተገልጋይ ፍሰትን ለማስተናገድ ተግዳሮት ሆኖበት ቆይቷል። ይህን ከፍተኛ የሆነውን የቀዶ ህክምና ተገልጋይ ፍሰትን ለማስተናገድ ሁለተኛውን የቀዶ ህክምና አገልግሎት ለመጀመር የሚያግዘውን ከሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ግዢ የተፈፀመላቸውን የOR table, Anesthesia machine, patient monitor, እንዲሁም ሌሎችን የህክምና መገልገያ ዕቃዎችና መድሀኒቶችን በሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ አማካኝነት ተረክቧል።
ድጋፍ ላደረገል የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በሆስፒታሉ ተገልጋዮች ስም ምስጋና እናቀርባለን🙏🏽