Alamura Primary Hospital , Hawassa

Alamura Primary Hospital , Hawassa Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Alamura Primary Hospital , Hawassa, Medical and health, Awassa.

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እያከውናቸው ከሚገኙ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች አካል የሆነ ‘በጎ አድራጎት ለጤናማ ማህበረሰብ’ በሚል መሪ ቃል በቀን 14/12/18 ዓ.ም የደም ግፊ...
21/08/2026

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል እያከውናቸው ከሚገኙ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎቶች አካል የሆነ ‘በጎ አድራጎት ለጤናማ ማህበረሰብ’ በሚል መሪ ቃል በቀን 14/12/18 ዓ.ም የደም ግፊት፤ የስኳር የማህጸን በር ጫፍ ካንሰር፤ የHIV AIDS፤ የቲቢ ፣የአይን ምርመራ ዘመቻ እንዲሁም በርኆቦት የበጎ አድራጎት ድርጅት በመገኘት የህክምና ድጋፍ አከናውኗል።
በሆስፒታሉ የህፃናት ህክምና ስፔሻሊስት ሀኪም በተመራው በጎ አድራጎት፣ የዕድገት ክትትል፣ ስር የሰደደ ሕመም፣የአጥንት ችግር ፣ በአይረን እጥረት የሚከሰት የደም ማነስ ፣አካል ጉዳተኝነት እንዲሁም ከውልደት የመጣ የአፈጣጠር ችግር የምርመራና የህክምና አገልግሎት በበጎ አድራጐት ተቋሙ ተጠልለው ላሉ ህፃናት ተደርጐላቸዋል።
እንዲሁም በታቦር ክፍለከተማ ፋራ ቀበሌ አዲሱ መናሀሪያ አካባቢ በተካሄደው ዘመቻ በርካታ የማህበረሰብ ከፍል አገልግሎት ያገኘ ሲሆን መርሀግብሩም በተለያዩ አዝናኝ ዝግጅቶች ታጅቦ ውሏል።

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ የአራተኛ ሩብ አመት ስብሰባና የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነ የአቅመደካማ ቤት እድሳት የማስጀመር መርሀግብር አካሄደ።**...
19/08/2026

‎የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ የአራተኛ ሩብ አመት ስብሰባና የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነ የአቅመደካማ ቤት እድሳት የማስጀመር መርሀግብር አካሄደ።
********************************
‎የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ስራ አመራር ቦርድ የ2018 ዓም የአራተኛ ሩብ አመት ስብሰባውን ና በሆስፒታሉ የሚከናወነውን የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት አካል የሆነ የአቅመደካማ ቤት እድሳት ማስጀመሪያ መርሀግብር አከናውኗል።
‎የሆስፒታሉን የቦርድ ስብሰባ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ፣ ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ሀላፊ እና የሆስፒታሉ ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አገና ነቶ መርተውታል።
‎በመድረኩ የ2018 ዓም አፈፃፀም፣ የ2019 እቅድ፣ በባለፈው ስብሰባ በቦርዱ ውሳኔ ተላልፎባቸው የነበሩ ተግባራትን የአፈፃፀም ደረጃ እና በቀጣይ ውሳኔ የሚፈልጉ ጉዳዮች ሪፖርት በሆስፒታሉ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ ቀርቧል።
ስራ አመራር ቦርዱም በተቋሙ የጤና አገልግሎት ዘርፎች የተመዘገቡ ውጤቶች፣ የታዩ ችግሮችና በቀጣይ ሊከናወኑ የሚገቡ ተግባራት ላይ ሰፊ ውይይት አካሂዷል።
ልዩ ትኩረት የሚሹ እና ውሳኔ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮችን የገመገመው ቦርዱ፣ አገልግሎቱን ማዘመን (ዲጂታላይዜሽን)፣ የተቋሙ የG+3 ህንፃ ስራን ማስጨረስ፣ የባለሞያ የስራ ቅጥር ፍላጎትን ማሟላትና የትራንስፎርመር ግዢ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች መካከል ናቸውም ብሏል።
የተቋሙ የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት አቶ አጋና ኔቶ ሆስፒታሉ በዓመቱ ያስመዘገባቸውን ውጤቶች አድንቀው፣ የተገኙ ስኬቶችን ማስቀጠልና ጉድለቶችን በአጠረ ጊዜ ለመፍታት በቅንጅትና በላቀ ቁርጠኝነት መስራት እንደሚገባ ገልፀዋል።

11/08/2026
የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ከክፍለተማና ከቀበሌ አመራሮች ጋር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባርና ፅዱ፣ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር ኢኒሼቲቭ አካል...
01/08/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንትና ሰራተኞች ከክፍለተማና ከቀበሌ አመራሮች ጋር የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባርና ፅዱ፣ ውብና ምቹ የስራ ከባቢን የመፍጠር ኢኒሼቲቭ አካል የሆነውን የፅዳት ዘመቻ በቀን 25/11/18 ዓ.ም በሆስፒታሉ ቅጥር ጊቢ እንዲሁም በሆስፒታሉ ዙሪያ ባሉ መንደሮች ህብረተሰቡን በማሳተፍ ከጠዋት 12:00 ጀምሮ በጋራ አካሂደዋል።

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የክረምት የበጐ ፈቃድ አገልግሎት ስራን አስጀመረ።*************************************** በቀን 23/11/18 ዓም በአላሙራ መጀመሪያ...
31/07/2026

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የክረምት የበጐ ፈቃድ አገልግሎት ስራን አስጀመረ።
***************************************
በቀን 23/11/18 ዓም በአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንት ፣የስራ ክፍል አስተባባሪዎች እንዲሁም የሆስፒታሉ ሰራተኞች በተገኙበት “በጎነት ለጤናችን” በሚል መሪ ቃል የክረምት በጎ ፈቃድ የጤናና ማህበራዊ አገልግሎት ማስጀመሪያ መርሀግብር ተደርጓል።
በዕለቱ የመክፈች ንግግር ያደረጉት የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ በንግግራቸው የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለሆስፒታላችን አዲስ አይደለም ያሉ ሲሆን የማስጀመሪያ መርሀግብሩ የነበሩትን የበጎነት ስራዎች በተጠናከረና በተቀናጀ መንገድ ለመምራት ያለመ ነው ብለዋል።
በመድረኩ የ2017 ዓም የተከናወኑአፈፃፀሞችና በ2018 የሚተገበሩ ስራዎች እቅድ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በዝግጅቱ ላይ የተሳተፉ ተሰብሳቢዎች የበጎነት አገልግሎት ላይ ተሳታፊ ለመሆን ከምንጊዜውም በላይ ተዘጋጅተናል ብለዋል።

💣🔥ለአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ደስ አለን/አላችሁ! 🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🧨አላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በሰራው የላቦራቶሪ ምዘና ...
30/07/2026

💣🔥ለአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ደስ አለን/አላችሁ! 🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🎆🧨
አላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በሰራው የላቦራቶሪ ምዘና ስታር ሶስት ላይ በመቀመጥ አንደኛ በመሆን የሰርተፊኬት ሽልማት ተበረከተለት።
********************************
የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የላቦራቶሪ ዳይሬክቶሬት የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ፣ የተሻለ ውጤት ላስመዘገቡ የጤና ተቋማት የዕውቅናና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ትውውቅ ባካሄደበት መድረክ የአላሙራ የመጀመሪያ ሆስፒታል ከክልሉ ከተመዘኑት ሆስፒታሎች ውስጥ 80.5% በማምጣት(Star ⭐⭐⭐) ደረጃ በማግኘት አንደኛ በመውጣት የሰርተፊኬት ሽልማት ተበርክቶለታል።

በመድረኩ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ክቡር ዶ/ር ዳመነ ዳባልቄ እንደገለጹት፣ 2018 በጀት ዓመት ለኢንስቲትዩቱ ከፍተኛ ስኬቶች የተመዘገቡበት ዓመት ሲሆን፣ ይህም ውጤት በየደረጃው ያሉ አመራሮችና ባለሙያዎች በቅንጅትና በተቀናጀ አሠራር በመሥራታቸው የተገኘ መሆኑን ገልጸዋል። ለስኬቱ አስተዋፅኦ ላደረጉ ሁሉም አካላትም ምስጋና አቅርበዋል።
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ በ2018 በጀት ዓመት የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ የጤና ጣቢያዎች፣ የመጀመሪያ ደረጃ፣ አጠቃላይና ስፔሻላይዝድ ሆስፒታሎች በተቋም ደረጃ የእውቅና ሽልማት ተሰጥቷቸዋል።
የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ባስመዘገበው ውጤት መሰረት በቀጣይ ዓመት በISO የሚወዳደር ይሆናል።

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 የአራተኛ ሩብ አመት የህዝብ ፎረም መድረክ ተካሄደ።***************************ዛሬ በቀን 22/11/18 ዓም አላሙራ የመጀመሪያ ደ...
29/07/2026

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 የአራተኛ ሩብ አመት የህዝብ ፎረም መድረክ ተካሄደ።
***************************
ዛሬ በቀን 22/11/18 ዓም አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ከሆስፒታሉ ተገልጋይ ማህበረሰብ ጋር የህዝብ ፎረም መድረክ አካሂዷል።
በዕለቱም የ2018 ዓ.ም የሆስፒታሉ አጠቃላይ አፈፃፀም ሪፖርት በሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ አማካኝነት ቀርቧል። በቀረበው ሪፖርት ዙሪያ ሰፊ ውይይት የተካሄደ ሲሆን ከተሳታፊዎችም አገልግሎት አሰጣጥን በተመለከተም ጥያቄና አስተያየት ቀርቦ መድረኩን በያዙት በአቶ ዮሴፍ ዮዌና በሆስፒታሉ ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ሄኖክ ኢሳያስ አማካኝነት ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል። በመጨረሻም የፎረሙ ታዳሚዎች በተቋሙ እየተሰራ ያለውን ስራ ያደነቁ ሲሆን መልካም አፈፃፀሞች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል።

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም የTB አፈፃፀምን ገመገመ።**************************************ዛሬ በቀን 11/11/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደ...
18/07/2026

አላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የ2018 ዓ.ም የTB አፈፃፀምን ገመገመ።
**************************************
ዛሬ በቀን 11/11/18 ዓ.ም የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ማናጅመንት ከሆስፒታሉ የTB አገልግሎት ባለሙያዎች ጋር በመሆን የ2018 ዓ.ም የTB አፈፃፀምን ገምግሟል።
በዕለቱ አጠቃላይ የአፈፃፀም ሪፖርት በክፍሉ አስተባባሪ ዶ/ር ትዕግስቱ ታዬ የቀረበ ሲሆን። በሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ አቶ ዮሴፍ ዮዌ መሪነትም ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
የዶት ቲቢ እንዲሁም መድሀኒት የተላመደ ቲቢ ህክምና አገልግሎት ማዕከል ላይ ያለው አፈፃፀም መልካም መሆኑ የተገመገመ ሲሆን በተለይ መድሀኒት የተላመደ ቲቢ ህክምና ለሀዋሳ ከተማ እንዲሁም ለሰሜን ሲዳማ ዞን አስተዳደር ለሚመጡ መድሀኒት የተላመደ ቲቢ ታማሚዎች ብቸኛ ማዕከል ሆኖ ለተገልጋዮች እፎይታን የሰጠ ሆኗል።

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የላቦራቶሪ ኬዝቲም የክህሎት ምዘና ፈተና ለላቦራቶሪ ባለሙያዎች ሰጠ።********************************በቀን 03/11/18 ዓ.ም በአላሙራ...
11/07/2026

የአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የላቦራቶሪ ኬዝቲም የክህሎት ምዘና ፈተና ለላቦራቶሪ ባለሙያዎች ሰጠ።
********************************
በቀን 03/11/18 ዓ.ም በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለላቦራቶሪ ባለሙያዎች የ6 ወር የክህሎት ምዘና ፈተና ተሰጥቷል።
ፈተናው የላቦራቶሪ ባለሙያዎችን የሙያ ብቃት ለመመዘንና በውጤት ደረጃ አጥጋቢ ያልሆኑ አፈፃፀሞችን በመለየት ጥራት ያለው አገልግሎት ለተገልጋይ ማህበረሰብ መስጠት እንዲችሉ በተገቢው የማብቃትና የድጋፍ ስልጠናዎችን ለማቅረብ ያለመ ነው።
ፈተናው በተዘጋጀው መርሃ ግብር መሰረት በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ቅጥር ጊቢ ተካሂዷል።
ጠንካራ የሙያ ብቃት ለተሻለ የጤና አገልግሎት!

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ስልጠና ተሰጠ።*********************************በሆስፒታሉ የስነምግባርና ፀረሙስና ክፍል አስተባባሪነት በአላ...
09/07/2026

በአላሙራ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ስልጠና ተሰጠ።
*********************************
በሆስፒታሉ የስነምግባርና ፀረሙስና ክፍል አስተባባሪነት በአላሙራ መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ስልጠና ከክልል በተጋበዙ አሰልጣኞች አማካኝነት ተሰጥቷል። በስልጠናው ወቅት የስራ ስነ-ምግባር፣ ተጠያቂነት፣ ግልፀኝነት፣ ሙስናን መከላከል፣ የግዢ ስርአት እና ለህዝብ የሚሰጥ አገልግሎት ጥራትን ማሻሻል በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ገለጻና ውይይት ተካሂዷል።

ተሳታፊዎችም ከስልጠናው ያገኙትን እውቀት በስራቸው ላይ በመተግበር ተቋሙ ከሙስና የጸዳ፣ ተጠያቂና ውጤታማ አገልግሎት እንዲሰጥ የበኩላቸውን ኃላፊነት ለመወጣት ቃል ገብተዋል።

Address

Awassa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Alamura Primary Hospital , Hawassa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share