29/05/2026
FDRE, Ministry of Labor and Skills
ካናዳ፤ ምዝገባም ሆነ ስምሪት አልተጀመረም! 🛑
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ዜጎች ክብራቸውና ደህንነታቸው ተጠብቆ በውጭ ሀገራት በሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ላይ በህጋዊ መንገድ እንዲሰማሩ ለማስቻል በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡
በአሁኑ ወቅት ዜጎች በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት (lmis.gov.et) ላይ በመመዝገብና ህጋዊ ሂደቶችን በመከተል፣ ኢትዮጵያ የሁለትዮሽ ስምምነት ወደተፈራረመችባቸው የሚከተሉት ሀገራት በህጋዊ መንገድ በመሰማራት ላይ ይገኛሉ፦
👉ሳውዲ አረቢያ
👉የተባበሩት አረብ ኢምሬትስ
👉ጆርዳን
👉ኳታር
👉ሊባኖስ
📍ወደ ካናዳ የሚደረግ የሥራ ስምሪት አለ?
የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መቀመጫውን ካናዳ ካደረገው "ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል" (FUTURE FIT INTERNATIONAL INC.) ጋር ስምምነት የፈጸመው በዋነኛነት ኢትዮጵያውያን ወጣቶች በዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ነው። ስምምነቱ በሚከተሉት ነጥቦች ላይ ብቻ ያተኩራል፦
• ከካናዳ ኮሌጆች ጋር በመተባበር ተማሪዎችን በዓለም አቀፍ የሥራ ገበያ በሚፈለጉ ክህሎቶች ማሰልጠን፤
• ብቁ የሆኑ ተማሪዎች በካናዳ በሚገኙ የትምህርትና ስልጠና ተቋማት የነፃ ትምህርት ዕድል እንዲያገኙ ማመቻቸት።
⚠️ ከፍተኛ ጥንቃቄ ይደረግ!
ከዚህ ስምምነት ውጪ፦
✅"ሚኒስቴሩ ወደ ካናዳ ህጋዊ የሥራ ስምሪት ጀምሯል" በማለት የተሳሳተ መረጃ ከሚሰጡ፤
✅"ወደ ካናዳ እንልክዎታለን" በማለት ከፍተኛ ገንዘብ ከሚጠይቁ፤
✅"ከሚኒስቴሩ ህጋዊ ውክልና ተሰጥቶናል" ከሚሉ አጭበርባሪዎች ራሳችሁን ጠብቁ!
📍ምን ማወቅ ይኖርብዎታል?
✍️ከፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል ጋር የተደረገው ስምምነት ወደ ተግባር ሲገባ፣ ዝርዝር መረጃው በሚኒስቴሩ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እና በብሔራዊ ሚዲያዎች ብቻ ይፋ ይደረጋል።
✍️ለዚህ ፕሮግራም ተጠቃሚ ለመሆን ምንም ዓይነት ክፍያ መፈጸም አይጠበቅብዎትም! ክፍያ የሚጠይቁ አካላት ሁሉ አጭበርባሪዎች መሆናቸውን ይወቁ።
✍️አጠራጣሪ እንቅስቃሴዎችን ሲመለከቱ ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ( 9138 በነፃ የስልክ መስመር ወይም [email protected] ) እና በአቅራቢያዎ ለሚገኙ የህግ አስከባሪ አካላት ይጠቁሙ።
🚨ትክክለኛ መረጃ ለማግኘት ይፋዊ አድራሻዎቻችንን ብቻ ይጠቀሙ፦
ግንቦት 19/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
Official Website: mols.gov.et
Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE
Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial
TikTok: tiktok.com/
Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር
WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYI