Dr Timothy

Dr  Timothy I'm here to make the difference

🚨 ሰበር እና ልብ ሰባሪ | የሞራል ኪሳራችን ማሳያ፡ ለ35 ዓመታት ሀገር ያገለገሉት አንጋፋ ባለሙያ በአደባባይ ተደበደቡ!ይህ የአሁኑ ትውልድ ምን ያህል የሞራል፣ የስነምግባር እና የግብረገብ...
11/04/2026

🚨 ሰበር እና ልብ ሰባሪ | የሞራል ኪሳራችን ማሳያ፡ ለ35 ዓመታት ሀገር ያገለገሉት አንጋፋ ባለሙያ በአደባባይ ተደበደቡ!
ይህ የአሁኑ ትውልድ ምን ያህል የሞራል፣ የስነምግባር እና የግብረገብነት ክሳራ ውስጥ እንደገባ የሚያሳይ እጅግ አሳዛኝ እና ፀያፍ ድርጊት ተፈፅሟል። የዚህ ልብ ሰባሪ ክስተት ሰለባ የሆኑት አቶ ዋቆ ከዲር የተባሉ አንጋፋ የጤና ባለሙያ ናቸው። እኚህ የዕድሜ ባለፀጋ አገልግሎታቸውን በክብር አጠናቀው የጡረታ መብታቸውን ለማስከበር ሰነዶቻቸውን በማደራጀት ላይ እያሉ፣ በባሌ ሮቤ ከተማ መናኸሪያ ውስጥ ማንነታቸው ባልታወቁ ወጣቶች አሰቃቂ ድብደባ ተፈፅሞባቸዋል።
አቶ ዋቆ ከዲር ለ35 ተከታታይ ዓመታት በቄለም ወለጋ ሆስፒታል፣ በጎባ ሆስፒታል፣ በጊኒር ሆስፒታል እና በራይቱ ጤና ጣቢያ ህዝባቸውን ሲያገለግሉ የቆዩ ውድ የሀገር ባለውለታ ናቸው። ህይወት አድነው፣ በሽተኛ አስታመው እና ሀገርን በታማኝነት አገልግለው ለጡረታ ሲበቁ፤ የህይወት ዘመን ድካማቸው ሽልማት በአደባባይ መደብደብ እና መዋረድ መሆኑ የደረስንበትን የህሊና መሞት ፍንትው አድርጎ ያሳያል።
ይህንን ዘግናኝ ድርጊት የፈፀሙት ወጣቶች ከሌላ ፕላኔት የመጡ ሳይሆኑ፣ የዚሁ ማህበረሰብ እና ስርዓት ውጤቶች ናቸው። ህግ በማይከበርበት ማህበረሰብ ውስጥ ህግ የማያከብር ትውልድ መፈጠሩ የፀሀይ ብርሃን ያህል ግልፅ ነው። የሞራልና የስነምግባር ተቋማት የራሳቸውን ኃላፊነት መወጣት ሲያቅታቸው፤ ጨካኝ፣ ለማንም የማይገደው፣ እጅግ ራስ ወዳድ እና የሞራል ስብእና የጎደለው አመፀኛ ትውልድ መፈጠሩ የማይቀር እውነት ነው።
ለዚህ አሳሳቢ የትውልድ ውድቀት ደግሞ ቤተሰብ፣ ጎረቤት፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የፖለቲካ መሪዎች እና የሃይማኖት አባቶች በሙሉ ተጠያቂዎች ናቸው። በጥቂት መልካም ሰዎች ብንፅናናም፣ ከአገር ጫፍ እስከ ጫፍ እየታየ እና እየተሰማ ያለው የሞራል ስብራት ግን ሀገርን ወደ ባሰ አዘቅት ከመክተቱ በፊት ሁላችንንም ሊያነቃን ይገባል።

A Message for 🇪🇹Ethiopia 🐕 What Morocco’s Stray Dog Crisis Teaches EthiopiaRecently, Morocco has faced global outrage ov...
21/02/2026

A Message for 🇪🇹Ethiopia

🐕 What Morocco’s Stray Dog Crisis Teaches Ethiopia

Recently, Morocco has faced global outrage over reports of mass killing of stray dogs, allegedly linked to preparations for the 2030 World Cup.

Even though no court has punished Morocco yet, the country is already paying a serious price.

🌍 What consequences can a country face for mass dog killings?

❌ International shame and reputation damage

Countries accused of animal cruelty lose global respect. Media, NGOs, and the public label them as inhumane.

❌ Tourism and economic loss
Tourists avoid countries

associated with cruelty. Campaigns and boycotts reduce income and investment.

❌ Pressure from global institutions

Organizations like FIFA, the EU, and the UN may apply monitoring, conditions, or restrictions.

❌ Public anger and activism
International attention

strengthens local activists and increases internal pressure on governments.

📚 Lessons from Other Countries

Romania faced years of EU criticism after killing stray dogs. The problem only improved after switching to sterilization.

Brazil was forced to change its methods due to global pressure before major sports events.

Countries that continued killing failed to control rabies.

Countries that vaccinated and sterilized dogs succeeded.

🚨 The Scientific Truth (WHO)
Rabies cannot be controlled by killing dogs.

It is controlled by vaccinating at least 70% of the dog population and using sterilization and community education.

Mass killing: ❌ Does not stop rabies

❌ Makes the problem worse

❌ Damages a country’s image

🇪🇹 A Message for Ethiopia

What is happening in Morocco shows us one clear truth:

👉 Cruelty is no longer a “local issue.” The world is watching.

If Ethiopia continues mass poisoning and killing of dogs:The same international backlash will come.

Public health will not improve.

Our country’s image will suffer.

Humane solutions are not weakness.

They are intelligence, science, and responsibility.

📢

09/09/2025
Timothy brand shoes 0949781509Inbox me
15/08/2025

Timothy brand shoes 0949781509
Inbox me

Check out ’s video.

ይህች ቤታችን ነች!! የትውልድ ማረፊያ አብረን እንሰራት።
03/07/2025

ይህች ቤታችን ነች!! የትውልድ ማረፊያ አብረን እንሰራት።

Check out user1099814171659’s video.

አስደሳች ዜና ለሥራ ፈላጊዎች በሙሉ!!!አርባምንጭ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም (የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት) የጉምሩክ ኮሚሽን በአዲስ መልክ ከተደራጀ በኋላ ተ...
27/06/2025

አስደሳች ዜና ለሥራ ፈላጊዎች በሙሉ!!!

አርባምንጭ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም (የአርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት)

የጉምሩክ ኮሚሽን በአዲስ መልክ ከተደራጀ በኋላ ተቋማዊ አቅምን ከመገንባት፣ አገልግሎት አሰጣጥን ከማሳለጥ፣ የህግ ተገዥነትን ከማረጋገጥ እና ገቢን በብቃት ከመሰብሰብ አንጻር አበረታች ድሎችና ዉጤቶች እያስመዘገበ ይገኛል፡፡

ስለሆነም ኮሚሽኑ የተጣለበትን ከፍተኛ ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት እንዲያስችለው በቅርቡ ሰርቶ ባጠናቀቀው ተቋማዊ አደረጃጀት ማሻሻያ ላይ ብቃት ያለው የሰው ሀይል ለማሟላት በተሰጠው ኮታ መሠረት ከክልሎች መልምሎ ለመቅጠር ዝግጅቱን አጠናቋል።

በዚህ መሠረት በኮሚሽኑ ስር በሚገኙ በማናቸውም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ወይም መቅረጫ ወይም መቆጣጠሪያ ጣቢዎችና በየትኛውም ዓይነት የአየር ፀባይ ውስጥ 24 ሰዓት 7 ቀን (24/7) ለማገልገል ፍቃደኛ የሆነች፣

በ2014፣ 2015፣ 2016 እና 2017 የትምህርት ዘመን ከመንግስት ዩኒቨርሲቲ ወይም ህጋዊ ዕዉቅና ካላቸዉ ከግል ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያ ዲግሪ የተመረቀ/ች፣

በኮሚሽኑ የሚሰጠውን መግቢያ ፈተና ማለፍ የሚችል/የሚትችል፣ በኮሚሽኑ የሚሰጡ ስልጠና መውሰድ የሚችል/የሚትችል ከዚህ በታች በተቀመጠው ዝርዝር መስፈርቶች መሠረት መመዝገብ ትችላላችሁ።

ማሳሰቢያ፦ ተመዝጋቢዎች ስመጡ የአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ ቀበሌ ነዋሪ ስለመሆናቸው የምገልጽ ማንነታቸውን የሚገልፅ መታወቂያ መያዝ ያለባቸው ሲሆን፣ ምዝገባው ከዛሬ ጀምሮ 3 ተከታታይ የሥራ ቀናት በወረዳው አስተዳደር ጽ/ቤት መሆኑን እንገልፃለን።

External Vacancy annocment from Addis Ababa City of Revenue office.[በዜሮ አመት እና በልምድ]- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ክፍት የስ...
26/06/2025

External Vacancy annocment from Addis Ababa City of Revenue office.
[በዜሮ አመት እና በልምድ]- የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ ክፍት የስራ ቦታ ማስታወቂያ

Deadline: July 3, 2025

ዘማሪት የምስራች ጨጓራዋ አከባቢ ከነበረው 4ኛ ደረጃ ካንሰር ተፈውሳ ነበር፣ ከጊዜያት በኋላ ቼካፕ ስታደርግ ጀርባዋ አከባቢ ሶስተኛው አጥንት ላይ እና ሳንባዋ ላይ ካንሰር ተገኝቶባት ከባድ ...
02/06/2025

ዘማሪት የምስራች ጨጓራዋ አከባቢ ከነበረው 4ኛ ደረጃ ካንሰር ተፈውሳ ነበር፣ ከጊዜያት በኋላ ቼካፕ ስታደርግ ጀርባዋ አከባቢ ሶስተኛው አጥንት ላይ እና ሳንባዋ ላይ ካንሰር ተገኝቶባት ከባድ ሳል ታክሎበት ፅኑ ሕሙማን ክፍል እንድትገባ ተደርጎ ነበር ዛሬ የተሰማው ዘማሪት የምስራች ህይወቷ ማለፉ ነው።

ለመላው ቤተሰቦቿ ወዳጆቿ መጽናናትን እንመኛለን።

🔥🔥🔥  የኢየሱስ የአገልግሎት ፈለግ❗️ "ከእኔ ተማሩ እኔ  የዋህ በልቤም ትሑት ነኝ"  (ማቴ. 11:29)🎯 የተሰቀለው ትሑት  መሲህ፣ የእምነታችን፣  የአገልግሎታችን፣ የሕይወታችን  መሪና ...
31/03/2025

🔥🔥🔥 የኢየሱስ የአገልግሎት ፈለግ❗️
"ከእኔ ተማሩ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝ" (ማቴ. 11:29)
🎯 የተሰቀለው ትሑት መሲህ፣ የእምነታችን፣ የአገልግሎታችን፣ የሕይወታችን መሪና መመሪያ ነው። የተጠራነው በሁሉም የእርሱን ሕይወትና የአገልግሎት ፈለግ እንድንከተል ነው።

🎯 የአዲስ ኪዳን አገልጋይ ከቅባቱ ይልቅ የቀባውን፣ ከስጦታው ይልቅ ሰጪውን፣ ከሹመቱ ይልቅ የሾመውን፣ በእርሱ ከሚገለጥ ጸጋ ይልቅ የጸጋ ሁሉ ምንጭ፣ ከመልዕክቱ ይልቅ የላከውን፣ ከራስ ስምና ከብር ይልቅ ጌታን ያስቀድማል። ይከተላል። ይመስላል። ደግሞም ያሳያል። ከዚህ ወጪ ከሆነ ግን ከቃሉ ጋር ይጋጫል። ይሰበራል። መጨረሻውም አያምርም። ለብዙዎች የመሳት፣ ለቤተክርስቲያን የመታወክ፣ የትውልድ መረን የመሆንና የክርስቶስም ሰም የመሰደብ ምክንያት ይሆናል። ይህ እንዳይሆን እንደ ጌታችን ዝቅና ዝግ ብለን፣ በትህትና፣ በፍቅርና ራስን በማዋረድ መስቀላችንን ተሸክመን እንከተለው። ደግሞም በፍቅር እናገልግለው። አገልግሎት ለራስ ተሰውረን ክርስቶስን የማሳየት መድረክ እንጂ ለመታየት የምንዋደቅበት አደባባይ አይደለም።

🎯 የእኛ ክብር አገልግሎታችን፣ ስማችን፣ ሹመታችን፣ አጀብ ማስከተላችን ሳይሆን የእርሱ መሆናችን ነው። ስለዚህ እርሱ ለስሙ ክብር በእኛ ባደረገውና በሠራው ለመክበር አንቋምጥ። እርሱን እንጂ ራሳችንን ለማክበርም ሆነ ለማስከበር አልተጠራንምና።

🎯 እርሱ በመንፈሱና በጸጋው ለእኛና በእኛ አልፎ ያደረገውን እንጂ ለእርሱ ያደረግንለትን ለማውራት አንቸኩል። ከእኛ የሆነ ምንም የለምና።

🎯 ዝቅ ብሎ የሚሸት የሰውን እግር ያጠበው ቅዱስና ትሑቱ ጌታ ለሌሎች መባረክና መታነጽ በአደራ የሰጠንን ጸጋ ለስሙ ክብር ለቤተክርስቲያን መታነጽ እናገልግልበት እንጂ ልዩ የመሆናችን፣ ከሌሎች የመሸላችንና የመብለጣችን ምልክት አድርገን በፍጹም አንቁጠር። እንደ ሰይጣን በትዕቢት ወጥመድ እንዳንወድቅ እንጠንቀቅ። "ፍራ እንጂ የትዕቢትን ነገር አታስብ" (ሮሜ.11:20) ተብለን ታዘናልና።

🎯 በጸጋው፣ በቃሉና በመንፈሱ ብርታት የገነባነውን አገልግሎት በትቢዕትና በእኔነት መንፈስ እንዳናፈርስ እንጠንቀቅ።

ተባረኩ
በወንድም ጸጋአብ በቀለ የተፃፈ
🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥🔥

ጌታ ሆይ እባክህን ትሑታን አድርገን። አሜን።

ፖሊስ አገልጋዮችን ከማጀብ እንዲታቀብ ተጠየቀ‼የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ካውንስል ፖሊስ አገልጋዮችን ከማጀብ እንዲታቀብ ጠይቋል።ኮንፍረንስ አስመልክቶ በጦር መሳሪያ አንድን አ...
27/03/2025

ፖሊስ አገልጋዮችን ከማጀብ እንዲታቀብ ተጠየቀ‼

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ካውንስል ፖሊስ አገልጋዮችን ከማጀብ እንዲታቀብ ጠይቋል።

ኮንፍረንስ አስመልክቶ በጦር መሳሪያ አንድን አገልጋይ ማጀብ እንደ ወንጌል አማኝ በፍፁም ተቀባይነት የሌለው ከአስተምሮት ውጪ መሆኑን የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ካውንስል እወቁልኝ ብሏል።

የካውንስሉ ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑት ፓስተር
ጌትነት ለማ በሰጡት መግለጫ የመንግስት አካላት ለአንድ አገልጋይ ፖሊስ አሰልፈው፣ መሳሪያ አስታጥቀው፣ አጀብ ፈጥረው ግርግር በማድረግ የሆነ አካል ወደ ከተማው የገባ የሚያስመስሉት ነገር ተገቢ እንዳልሆነ ተናግሯል።

እጀባው ትርጉም አልባ ነው ከመፅሐፍ ቅዱስ ውጪ ነው በጦር መሳሪያ መታጀብ ትርጉሙ ሌላ ነው ፍርሃት ሲኖር ነው መታጀቡ የሚመጣው፣ አገልጋዩ ከህዝብ የተበደረው ገንዘብ ሲኖር ችግር የሚፈጥርብኝ ህዝብ ይኖራል ብሎ ሲፈራ ነው በፖሊስ የሚታጀበው እንጂ ወንጌል ለመስበክ ከሆነ እጀባ አያስፈልገውም ብለዋል።

በተደጋጋሚ እንደዚህ የሚያደርጉ አገልጋዮች በፅሁፍ፣ በአካል ማስጠንቀቂያ ሰጥተናል በቅርቡ እርምጃ ወስደን መግለጫ እንሰጣለን ብለዋል።

መጋቢት 11 ቀን ነብይ ኢዩ ጩፋ ወደ ሀዋሳ ሲመጣ የመንግሥት ፖሊስ እና ሙሉ ማርሻ ባንዱ አቀባበል ማድረጉ "መንግሥት እና ሀይማኖት የተለያዩ ናቸው" የሚለውን የህገመንግስት ድንጋጌ ጥሷል በሚል አነጋጋሪ እንደነበር ይታወሳል።

Address

Wolaita S**o
S**o

Telephone

+251949781509

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Dr Timothy posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Practice

Send a message to Dr Timothy:

Share

Category